Thursday, February 6, 2014

ሰበር ዜና (Breaking News)

ሰበር ዜና (Breaking News)

04/02/2014 ማክሰኞ ዕለት አባ ግርማ ከበደ፤ ሁለት ሌሎች ካህናትና እንዲሁም ሌሎች ኢትዮጵያውያን ከሁለት የውጪ ሰዎች ጋር በመሆን ለንደን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ ረጅም ሰዓታትን የፈጀ ስብሰባ ማካሄዳቸው ታወቀ።

በኤምባሲው /ቤት ውስጥ የተካሄደውን ስብሰባ የመሩት አንባሳደሩ ሲሆኑ በስብለባው ላይ የተገኙትም አባ ግርማ ከበደ፤ ሁለት ሌሎች ካህናት፤ አቶ ግርማ /ማርያም (በቅጽል ስሙ ግርማ ቡፋው/ ውሸታሙ) የእነ አባ ግርማ ጠበቃ ነኝ የሚለው አቶ ስምረትና ሌሎች ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በድምሩ 12 ኢትዮጵያውያንና ሁለት ፈረንጆች ነበሩ።
ስብሰባው የተካሄደው ከቀኑ 1pm ጀምሮ አስከ አመሻሹ ድረስ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል።

ስብሰባው ያተኮረበትም UK ኗሪ የሆነው ስደተኛ ኢትዮጵያዊ ጥሮና ግሮ ያቆማትንና ለከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ያበቃትን ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን አስተዳደሯንና ንብረቷን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያው አገዛዝና በደጋፊዎቹ ቁጥጥር ሥር ለማዋል ከበላይ አካል የመጣውን መመሪያ በመግለጽና የተጀመረውን ሥራ ለማሳካት የሚያስችሉ ነጥቦች አንስቶ በመምከር ላይ ነበር።

መላው UK የምትኖሩ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ሁሉ።

ዛሬ የኢትዮጵያው አገዛዝ በኤምባሲው አማካኝነት ጥራችሁና ግራችሁ ሃብትና ጉልበታችሁን በማስተባበር የገዛችሁትን ቤተ ክርስቲያናችሁን ለመንጠቅ አይኑን አፍጥጦ ጥርሱን አግጥጦ መጥቶባችኋል!!

ዛሬ ይህችን የስደተኛው ኢትዮጵያዊ አንጡራ ሃብት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን ከኢትዮጵያው አገዛዝ ጣልቃ ገብነት ለማትረፍ በቁርጠኝነት ተነስታችሁ ካልታገላችሁ፤ በቀጣዩ የኮሚኒቲ ማዕከላት፤ ከዛም አገዛዙ ድምጽ አልባ ላደረገው የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጽ ሆነው ለመከራከር የሚጥሩ የፓለቲካም ይሁን የሲቪክ ማህበራትና የጽዋ ማህበራት ሳይቀሩ በአገዛዙና በደጋፊዎቹ ቁጥጥር ሥር ከመዋል አይተርፉም።

ይህም ብቻ አይደለም ይህ የሰብዓዊ መብት ረገጣ ባህርን ተሻግሮ መጥቶ በነጻነት ሃገር እግር መትከል ከጀመረ በመጨረሻ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ቤት በር እየተንኳኳ የኢትዮጵያውን አገዛዝ የማትደግፍ ከሆነ አሳርህን ትበላለህ እየተባለ በነጻነት ሃገር የባርነት ኑሮ ለመኖር የሚገደዱበት ደረጃ ላይ ሊደርስ እንደሚችል አበክሮ መገንዘብ ይገባል።
በነፃነት ሃገር እየኖረ ቤተ ክርስቲያኑንም ሆነ ራሱንና ቤተ ሰቡን ከሰብዓዊ መብት ረጋጭና አንባ ገነን መንግሥት ነጻ ማውጣት ያልቻለ ህብረተሰብ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሕዝቤን ከአገዛዙ የጭቆና ቀንበር ነጻ ለማውጣትና ሰብዓዊ መብቱን ለማስከበር እታገላለሁ እያለ ቢለፍፍ በራስ ከመቀለድ ያለፈ ቁም ነገርነት ሊኖረው አይችልም፤ ምክንያቱም ራሱን ነፃ ያላወጣ ሌላውን ነፃ ሊያወጣ ከቶ አይቻለውምና!!

ይህም በመሆኑ ዛሬ ነገ ሳትሉ ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ለማዳን በጽናት ቆመው ከሚታገሉ ኢትዮጵያውያን ወንድምና እህቶቻችሁ ጋር በቁርጠኝነት በመሰለፍ የሕግ የበላይነት ባለበትና ነጻነትና ዲሞክራሲ በሰፈነበት ሃገር እንደተቀረው ህብረተሰብ ሁሉ በነፃነት የመኖራችሁን ዋስትና ታረጋግጡ ዘንድ በእመቤታችን ስም ጥሪ እናቀርባለን።

ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቤተ ክርስቲያንን እናድን!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

Sunday, February 2, 2014

ye-yekkatit ilkit


The first and perhaps most grievous assault, which many Ethiopians of the time believed, was the deliberate introduction of rinderpest, the most devastating viral disease of cattle, to facilitate the colonization of a starving and exhausted populace.  Just prior to the Italian invasion of Ethiopia in 1888, a devastating epizootic of rinderpest was ignited by the introduction of three infected Indian cattle through the Ethiopian port of Massawa.  Rinderpest quickly engulfed the herds of Ethiopia, killing over 90 percent of the cattle and causing great mortality also in wild ruminant populations of buffalo, hartebeest, and antelope.  As a consequence, an estimated 30‑60 percent of the population of Ethiopia starved to death (Pankhurst, R., "The Great Ethiopian Famine of 1888‑1892: A New Assessment."  The Journal of the History of Medicine and Allied Sciences, (1966) Part I, pp. 95‑124; and Part II, 271‑294).

The story of the devastation of rinderpest is commemorated on the Ethiopian calendar as ye-yekkatit ilkit (the Annihilation of the month of Yekkatit).  Shortly thereafter the disease spread like wildfire to the entire continent of Africa, killing hundreds of millions of cattle and wild ruminants. Rinderpest still remains the number one cattle disease in Africa. 

It is at this juncture that Italy advanced from Massawa to conquer Ethiopia. But Emperor Menelik rallied his starving nation to confront the Italians at the Battle of Adwa; amazingly, he was able to defeat this European colonial power despite its modern military machine.  More miraculously, he did it while his people were struggling to survive the famine caused by rinderpest.  In addition to other political difficulties, rinderpest also sapped the energy of Menelik’s army, and he was prevented from crossing the Mereb River to dislodge the Italians from all territories of Ethiopia.  Thus, Mereb Millash remained occupied by the Italians.  They renamed it “Eritrea” on January 1, 1890, thereby creating for Ethiopia an enduring cancer that would eat away at the nation.   According to Donald L. Levine, the key to Menelik’s success was the strength of an army derived from multiethnic cooperation; it becomes obvious why the TPLF/EPLF has unleashed a divisive ethnic war in Ethiopia as soon as it grabbed power.