Monday, February 11, 2013

ፍቅርና አንድነት ያለው ህዝብ ጠላቱን ያሸንፋል



ሉሉ ከበደ

ባለፈው ሂትለርና የወያኔን መሪዎች ባነጻጸርኩበት ጽሁፍ ላይ መለስ ስብሀት በአማራው ህዝብ ላይ በሰፊው ሊያንቀሳቅሱ የሞከሩት እልቂት አንዴት በሚፈልጉት ልክ እንዳልገፋላቸው ሗላ ላይ እናወጋለን ብየ ነበር።

በአለማችን ያሉ ጤናማ መንግስታት በዜጎቻቸው መካከል የመብት ልዩነትና የዘር የቀለም መለያየት፤ ግጭት እንዳይኖር ያለመታከት ይሰራሉ። ይተጋሉ። በኢትዮጵያ ያለው የዲያቢሎሶች መንግስት፤ ሰው በዘሩ ተለይቶ እንዲታወቅ፤ እንዳይስማማም እንዲበላላም ለማድረግ በትጋት ሲሰራ ሀያ ሁለት አመታትን አስቆጠረ።

ስርአትን መቃወም አንድ ነገር ነው።ስርአቱን ወደ ጎን አድርጎ አንድን ክፍለ ህዝብ እንደስርአት ስሎ፤ የመደብ ጠላት አድርጎ፤ አእላፍ ቋንቋ የሚናገርን ሕዝብ ለድህነትህ፤ ለሗላቀርነትህ፤ ተጠያቂ፤ ጠላትህ፤ ያንን ቋንቋ የሚናገረው ዘር ነው ብሎ፤ ባንድ ወገን ላይ የጥላቻ ዘመቻ ማንቀሳቀስ ዘርን ለማጽዳት ከሚደረግ ትልምና እቅድ የተለየ አላማ አለው ማለት ያስቸግራል።

ገዢ መደቦች ለፈጠሩት ስህተት ወይም ወንጀል፤ እነዚያ ገዢዎች የወጡበት ክፍለ ህዝብ እንደ ጠላት ተቆጥሮ ትውልድ በማያቀው ጉዳይና በማይደግፈው ድርጊት እዳ የሚከፍልበት አንዳችም ምክንያት አይኖርም። ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት የህውሀት መሪዎች ስልጣኑን በጠመንጃ ተቆጣጥረው በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያደረሱት ላለው በደልና ወንጀል፤ ለራሱም የችግሩ ሰለባ የሆነው የትግራይ ህዝብ ተጠያቂ ነው የሚል አስተሳሰብ ያለው፤ የሀያ አንደኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያዊ ይኖራል ብየ አላምንም። ምንጊዜም በሀገርና በህዝብ ላይ ለሚፈጸሙ አስተዳደራዊ ወንጀሎች፤ ተጠያቂው በአፈሙዝም ይሁን በምርጫ ስልጣን የተረከበውን ቡድን በበላይነት የሚመሩት፤ የህጉም የፖሊሲውም፤ አውጪዎችና አስፈጻሚዎች በጣት የሚቆጠሩት መሪዎች ናቸው እንጂ፤ ያመሪ የወጣበት የህብረተሰብ ክፍል አይደለም። በተዋረድ እንደየስልጣን ደረጃቸውና ሀላፊነታቸው እስከታች አርከን የወንጀሉ ተሳታፊዎች በህግ ይጠየቃሉ። ሕዝብ ከደሙ ንጹህ ነው።

1983 ወደ ሗላ መለስ ብየ ልጀምረውና በአርሲ አርባ ጉጉ፤ በአሰቦት ደብረወገግ ገዳም፤ በበደኖ፤ እና በሌሎቹም አካባቢዎች ህውሀት ወደ ስልጣን አንደመጣ በአማሮች ላይ ሊያንቀሳቅስ የሞከረው ፍጅት የተፈለገውን ያህል ውጤት ሊያመጣ ያልቻለው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ለምእተ አመት ያካበተው ውህደት የፈጠረው፤ የወንድማማችነትና የአንድነት መንፈስ፤ አሸናፊ ሆኖ በመገኘቱ፤ ህብረተሰቡ ለዚያ መተላለቅ በቀላሉ ተነሳስቶ እነ መለስ ስብሀት ሚፈልጉትን ባለማድረጉ ነበር። ሌላው ምክንያት ታላቁ ያገር ልጅ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የመሩት እንባ ጠባቂ የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት፤ በዚህ ክፍለ ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን ሰቆቃና በደል፤ ወያኔ ይዞት የመጣውን የዘር ማጥፋት እቅድ፤ በያለሙ እንዲስተጋባ በማድረጉ፤ አሁን ያለው የአለም ተጨባጭ ሁኔታ ያንን ሊያስቀጥል የሚችል አለመሆኑን ጌቶቻቸው ስለ ነገሯቸው ሊቀጥሉበት አልቻሉም።
ወደ መጀመሪያው ሙከራቸው ልሂድና የመጀመሪያውን እልቂት ሊያንቀሳቅሱ የሞከሩት የህውሀትንና የኦነግ ወታደራዊ ካድሬዎችን በማሰማራት ነበር። ህውሀትና ኦነግ ያሰማሯቸው የሁለቱ ቡድን መልከተኞች ናቸው አንጂ በአርሲም በሀረርጌም ያን መተላለቅ የፈጠሩት አብሮ የሚኖረው ህብረተሰብ አልነበረም።

ለዚህም ማስረጃ በወቅቱ እዚያው አካባቢ ስለነበርን ሀረርጌ በአካል ህብረተሰቡ ውስጥ ተገኝተን በተለይም ህውሀት ግጭቱን ለማንቀሳቀስ ኢላማ ያደረጋቸው አማሮችና ኦሮሞዎች እንዴት በመተሳሰብ ያንን ሁኔታ እንዳሳለፉት እንድ ተጨባጭ ታሪክ አቀርባለሁ።

ሐረርጌ አንድ ገጠር አውራጃ ውስጥ አማሮች እየታደኑ በሚገደሉበት ሰሞን የህውሀትና የኦነግ ካድሬዎች ባንዲት ገበሬዎች መንደር አንዱን ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ ጎልማሳ በገዳይነት ሊመለምሉት እቤቱ ይመላለሳሉ። አስፈላጊ ነው ብለው ያመኑበትን የፖለቲካና የዘር ጥላቻ ትምህርት ለሳምንታት በቤቱ እየተመላለሱ ከሰጡት በሗላ መሳሪያ ያስታጥቁታል። ልብ ይሏል በዚያን ጊዜ እነሱን መቃወም የኦሮሞን ነጻነት መቃወም ተደርጎ እርምጃ ያስወስዳል። ያ ድሀ አርሶ አደር አስፈላጊው የፖለቲካ ትምህርትና መሳሪያ ከተሰጠው በሗላ የተነገረው ተልእኮ ባካባቢው የሚኖሩ አማሮችን ስለሚያውቅ እያደነ እራሱ እንዲገድል ነበር።እዚያው አጠገቡ አብሮ አደግ ጉረቤቱ የሆነ ሰው ይኖር ስለነበረ ሄዶ እንዲገለው ትዛዝ ይሰጠዋል። ይህን ብለውት ከቤት እንደወጡ እሱም አብሮ ይወጣና ቆይቶ ወደቤቱ ተመልሶ ይመጣል።

ከሰአታት በሗላ ተመልሰው ግዳጁን ተወቶ እንደሆነ ይጠይቁታል። እቤቱ የለም ይላቸዋል። አብሮ አደግ ጎረቤቱ ግን ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር እሳት ዳር ቁጭ ብለው ይጫወቱ ነበር። እነዛ የኦነግ እና የህውሀት አረመኔዎች ሲመጣ ጠብቆ እንዲገለውና ሪፖርት እንዲያደርግ ማስጠንቀቂያም ጭምር ሰተውት ይሄዳሉ። አሁንም ይህ አርሶ አደር ከቤት ወቶ እነሱ ሲሄዱ ተመልሶ ከቤቱ ይቀመጣል። በድጋሜ ተመልሰው መጡና ትዛዛቸው መፈጸሙን ሊያረጋግጡ “ገደልከው?” አሉት።

ያ ቅዱስ የኦሮሞ አርሶ አደር እንባውን እያፈሰሰ “…እባካችሁ ተውኝ .. ይህን ድሀ አብሮ አደግ ወንድሜን ግደል አትበሉኝ ። ይህንን የኔቢጤ ሚስኪን ብገድለው ድህነቱና ቅማሉ አንጂ ምን ይተርፈኝ መሰላቸሁ። ግደሉኝ ብትፈልጉ… አልገለውም..፡ “ በማለት ያሸከሙትን መሳሪያ ወዲያ ወረወረው። እነዚያ ካድሬዎች ያንን ድሀ አማራ ያን እለት ከነልጆቹ ይዘውት ሄዱ። ወዴት እንዳደረሷቸው ግን አይታወቅም።

በዚያን ጊዜም ሆነ አሁን ከሀያ ሁለት አመታት በሗላ ወያኔዎችም ሆኑ የተወሰኑ ኦነጎች ችግራቸው ለራሳቸው ተጭነውት የሚሰቃዩበትን በሽታ በቀጥታ በህብረተሰቡ ላይ ለማራገፍ ከመጣደፍ በቀር እዚያ የደረሱበት አካባቢም ሆነ በማናቸውም ጥግ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ “በእንዴት ያለ ሁኔታ ነው አብሮ መኖር የያዘው? ትስስሩና ፍቅሩ እምን ድረስ ነው? ውህደቱና ስምምነቱ እምንድረስ ነው ?” ብለው የህብረተሰቡን ሁኔታ ለማጥናት ጊዜ አይወስዱም።የኢትዮጵያ ህዝብ እነሱ በታወሩበት የዘረኝነት በሽታ ታውሮ የሚኖር ነበርም ነውም የሚመስላቸው።

በወቅቱ የታዘብኩትን ሌላ ገጠመኝ ላውጋ። እዚያው ሀረርጌ ውስጥ ነው። ጊዜዋም ያችው ቀውጢዋ ነበረች። አንዲት የወረዳ ከተማ ውስጥ ልዩ ልዩ ብሄረሰቦች ይኖራሉ። አብዛኛው ኦሮሞ ይሁን እንጂ አማራ፤ ጉራጌ፤ አፋር፤ከሶማሌ ብሄረሰብ ኢሳ የሚኖሩበት ከተማ ነች። እነዚህ ክፉ ሰዎች ገና ሁሉንም ተቆጣጥረው እንደጨረሱ ቢሆንም በደንብ አልተረጋጋም። ኦነጎችም እስር እስራቸው ይሉ ነበር። በዚች በማወሳት ትንሽ ከተማ ውስጥ አስተዳዳሪዎች ነን ብለው ኦነጎች ቢሮ ገባ ገባ ብለው የነበረበትና አለቆቻቸውም ከወያኔ ጋር ሽግግር ምክር ቤት ሽር ጉድ ይሉ የነበረ ጊዜ ነው። ክልሉ የኦሮሞ ስለሆነ እናስተዳድራለን ይሉን የነበሩት የኦነግ ታጣቂዎች አምስት ስድስት ትላልቅ የኝነት መኪና ሞልተው፤ ጠመንጃ ተሸክመው፤ ላይ ታች በከተማው ዥው ዥው ይሉ የነበሩቱ እያስተዳደርን ነው ብለው ቢሮ በገቡ በሶስተኛው ቀን፤ ኦሮምኛና ትግርኛ እንጂ አንዲት የአማርኛ ዘፈን እንዳንሰማ በማለት “ይህንን ግም አፍ” ከእንግዲህ ሲያዘፍን የተገኘ እርምጃ ይወሰድበታል ብለው ሖቴሎችና ሻይቤቶች ሳይቀሩ አማርኛ እንዳያዘፍኑ ትዛዝ አስተላለፉ። ጠቅላላው የከተማዩቱ ነዋሪ ፈራ። ወዲያው ደግሞ ቀጠሉና በአራተኛው ይሁን በአምስተኛው ቀን የአማርኛ ቋንቋ እንዳይነገር መመሪያ ሰጡ።

በዚህን ጊዜ ነው የከተማዩቱ ኦሮሞ ነዋሪዎች ከሌሎቹ ነዋሪዎች ጎን በመቆም “አይዞአችሁ። እነዚህ ኦሮሞዎች አይደሉም። ምን እንደሆኑም አናውቅም። ተረጋጉ ።” ብለው በቀጥታ ከነዚያ ሰዎች ጋር መላተም የጀመሩት። በከተማዩቱ የኢሳ ብሄረሰብም ይኖራል ብያለሁ። ለገበያ ይመላለስባታል። እነሱም ክልሉ የኛነው ይሉ ነበረና ይህ ሁሉ ሲሆን ለካንስ ኢሳዎች በጥሞና እየተከታተሉ “ምንድናቸው?” ብለው ይጠይቃሉ። “ኦነግ” ይሏቸዋል። “ኦነግ ምንድነው? ምን ያደርጋሉ እዚህ?” “የኦሮሞ ነጻ አውጭ ናቸው ያስተዳድራሉ” ተባሉ።

በመሰረቱ ከጥንት ጀምሮ የኢሳ ብሄረሰብና ኦሮሞ ይጣላሉ። ልማዳዊ አለመግባባት አለ። የኢሳ ብሄረሰብ ዘላን ከብት አርቢ ስለሆነ ሳር ፍለጋ ከብቶቹን ከቦታ ቦታ በሚያንቀሳቅስበት ጊዜ ኦሮሞዎች የሚኖሩበትንም አካባቢ መድረሱ ስለማይቀር፤ የተሰማሩ ከብቶችን ካገኘ እየቀማም እየዘረፈም ከመንጋው ቀላቅሎ ይዞ መሄድ የተለመደ ነገር ነው። ለማስመለስ መሳሪያ ሳይቀር ይመዘዛል። ሰውም ይሞታል።

እና ታዲያ አሁን በማወሳት ከተማ ውስጥ ሕዝቡን መከራ እያበሉ ያሉትን የኦነግ ተዋጊዎች “ይህ ክልሉ የኛ ስለሆነ ለቃችሁ ውጡ” ብለው ሽማግሌ ይልኩባቸዋል። ጌታዋን የተማመነች በግ ላቷን ደጅ ታሳድራለች እንደተባለው ወይም ወያኔ አለልን ብለው ወይም ደግሞ ኢሳ ተዋጊ መሆኑን አለማወቅ፤ ማስጠንቀቂያውን ከእቁብ ሳይቆጥሩ ሰዉን ማሸበራቸውን ቀጠሉ። በዚህን ጊዜ ኢሳ ጦርነት ሊከፍት ከየገጠሩ እየተጠራራ በከተማዩቱ ሰፍሯል። እነ ኦነግም በበርካታ የጭነት መኪኖች ሞልተው ላይ ታች ይላሉ። ጥቂት የወያኔ ወታደሮች ከተማው ጥግ ሰፍረው የሚሆነውን ይከታተላሉ። ጣልቃም አይገቡም።

አንድ ቀን ጠዋት ማለዳው ላይ ያቺ ትንሽ ከተማ በቀላል ነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያ ተኩስ ልትፈነዳ ደረሰች። ለሁለት ሰአት አካባቢ ሞቅ ያለ ተኩስ ከተሰማ በሗላ፤ መልሶ ጸጥ ለጥ ረጭ አለ። እስከቀትር ድረስ ሰውም ከቤት አልወጣ ከተማዋ ጭር እንዳለች ዋለና ሗላ ላይ የኢሳ ብሄረሰብ ወዲያ ወዲህ ሲል ሁላችንም ከተሸሸግንበት ወተን የሆነውን እናጠያይቅ ጀመር። አዎ እነዚያ ሰዉን ያምሱት የነበሩ የኦነግ ጂሎች መሬት ይግቡ ሰማይ የደረሱበት አይታወቅም። የሞተው ሞቶ የቀሩት ድራሻቸው ጠፍቷል። ወዲያውኑ በየሆቴሉ በየሻይቤቱ የአማርኛ ዘፈን ይሰማ ጀመር። ሰውም ጮክ ብሎ አማርኛ ያወራ ጀመር።

የከተማዪቱ ኦሮሞኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች በዚያን ሰሞን ለቀረው ህዝብ ያሳዩት አጋርነትና ተቆርቋሪነት፤ ያሳዩት ወገንተኝነትና አብሮነት የዘር ድርጅት መሪዎች እጅግ ብዙ ሊማሩበት የሚያስችል ክስተት ነበር።

ታዲያ ግጭቱ ከተከሰተ በሗላ ምን ይሆን ትተው የሄዱት፤ በየቢሮው ጥለውት የሄዱ ሰነድ ካለ ምን ይሆን እቅዳቸው አልንና የተወሰንን ሰዎች በየቢሮው ገብተን መበርበር ጀመርን። ያገኘነው አስደንጋጭ ነገር ቢኖር በከተማዋ ነዋሪ የሆኑ፤ ነዋሪው በጠቅላላ የሚያከብራቸው፤ የሚወዳቸው፤ ያገር ሽማግሌዎች የሞተን የሚቀብሩ፤ የታመመን የሚያስታምሙ፤ የተቸገረን የሚረዱ፤ አስራ ስድስት ነዋሪዎች ስም ዝርዝር እንዲገደሉ በቃለጉባኤ ተፈርሞበት ተቀምጧል። ለኦሮሞ ህዝብ ነጻነት እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ነፍጠኞች ስምዝርዝር ይላል። የሚደንቀው ደግሞ ከነዚያ ሰዎች አራቱ ኦሮሞዎች ነበሩ።

ያቺ የኢሳ ብሄረሰብ ያስነሳት አጭር ጦርነት የነዚያን ንጹሀን ዜጎች ህይወት ለማትረፍ በቃች።ሕህቡንም ከመራር ሀዘን አዳነችው።

የኢትዮጵያ ህዝብ እንደነዚህ አይነት በሽተኞችን ይዞ ነው የሚጓዘው። ይህ የዘር ጥላቻ፤ ይህ የዘር ፖለቲካ፤ የወያኔን መሪዎችና መሰሎቻቸውን ለጊዜው ተጠቃሚ ሊያደርጋቸው ይችላል። በረጅም ጊዜ ጦሱ ግን የሚያጠፋቸው ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘመናት ያካባተው፤ ያዳበረው አብሮ የመኖር የአንድነትና የመተሳሰብ መንፈስና ባህል ምንጊዜም በውስጡ ያለ በመሆኑ አንድ ቀን እነዚህን የዘር ልክፍተኞች በቃችሁ እንደሚላቸው ጥርጥር የለውም። የኢትዮጵያን ሀብት ዘርፈን የ ኢትዮጵያን ህዝብ በትነን የራሳችን መንግስት እናቆማለን ብለው ለሚቧችሩ ወዮ ለነሱ ይህ ሕዝብ አንድ ሆኖ በቃ ያለቀን።በመጨረሻዋ ሰአት ወዮ ለዘረኞች!

በስደት በምንኖርበት የባእድ አገር ጽንፈኛ የዘር ፖለቲካ አቀንቃኞች ለልጆቻቸው እንዴት ጥላቻን እንደሚያስተላልፉ የሚያመለክት አንድ ገጠመኝ ላክል።ይህንን ታሪክ ያጫወተኝ ሰው ነገሩ ለርሱ ብዙም ክብደት አልሰጠውም። የልጅ ነገር ብሎ እየሳቀ ነው የነገረኝ። እኔ ግን ከልጅ ነገርነቱ ባሻገር ነው የከፋ ነገር የታየኝ። ላንባቢያን ባካፍለው ሁላችንም እንማርበታለን ብየ አሰብኩ።

ሁለት ህጻናት ወንዶች ልጆች እድሜያቸው አስራ አንድ አመት የሆኑ ትምህርት ቤት ተከፍቶ አንድ ክፍል ይመደባሉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን ናቸው። ያንኑ እለት በእፈፍት ሰአታቸው እግር ኳስ ሊጫወቱ እየተሯሯጡ ኳስ ሜዳ ገብተው ጥቂት እንደተጫወቱ ለማረፍ ወደሜዳው ጥግ ሄደው ሳር ላይ ቁጭ እንዳሉ ይተዋወቁና ጎን ለጎን ተንጋለው ወሬ ይጀምራሉ። ከየት እንደመጡ ይጠያየቃሉ። አንደኛው ከኢትዮጵያ አንደመጣ ሲነግረው ሌላኛው ከኦሮሚያ ነው የመጣሁት ይለዋል። ሁለቱም የኦሮሞ ብሄረሰብ ተወላጆች ናቸው። ይህ ከኢትዮጵያ ነው የመጣሁት የሚለው ልጅ “ ኦሮሚያ የት ነው” ይለዋል አዲሱ ጓደኛውን።

“ እሩቅ አፍሪካ ውስጥ ነው።” ይመልሳል የኦሮሚያው ልጅ
“ እዚህ አገር ከመጣህ ተመልሰህ ሄደሀል?”
“ አዎ ሰባት አመት የነበርኩ ጊዜ ሄጄ ነበር”
“ እኔም ስድስት አመት የነበርኩ ጊዜ አባቴ ወስዶኛል። ኢትዮጵያ ብዙ ደስ ብሎች አሳለፍኩ…ኦሮሚያ ከኢትዮጵያ በየት በኩል ነው?”
ተጠያቂው ህጻን ኦሮሚያ በየት በኩል ነው ለሚለው ጥያቄ መልስ ከመስጠቱ በፊት “አማራ ነህ?” ይለዋል። ከኢትዮጵያ መጣሁ የሚለው ልጅ ብሄሩንም አያውቅምና “ እኔ አንጃ “ ይላል።

ያም ቀበል ያደርግና “ ኢትዮጵያ የአማራዎች አገር ነው። ጥሩ አይደለም። ኦሮሚያ ጥሩ ነው። “ ይላል።
ብዙም አልተግባቡ ወደጨዋታቸው ይመለሳሉ። ይህ ከኢትዮጵያ ነው የመጣሁት የሚለው ልጅ ይህንን ታሪክ ለወላጆቹ ይነግርና “ኦሮሚያ የት ነው አዲስ ጓደኛ አገኘሁ” ይጠይቃል አባትን። አባትም ኦሮሚያ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ አንድ ክልል መሆኑን ያስረዳና የሚኖሩበት አገር ካናዳን እንደምሳሌ አድርጎ ፕሮቪንሶቹን እየጠራ እንደ አንዱ እንደማለት ነው ካለ በሗላ “ሁለታችሁም ኢትዮጵያውያን ናችሁ። ወንድማማቾች ናችሁ። ጥሩ ጓደኛ አግኝተሀል እንኳን ደስ ያለህ” ይለዋል።

ልጅ ይህንኑ ካባቱ የተነገረውን በሁለተኛው ቀን ትምህርት ቤት ሲሄድ ለአዲሱ ጓደኛው ያስረዳና በጓደኝነታቸው እንደሚቀጥሉ ይነግረዋል።

ያኛው ህጻን ግን ባልተጠበቀ መልኩ የሚያስከፋ መልስ ይሰጠዋል። “…ኖ!..ኖ! ከንግዲህ አንተ የኔ ጓደኛ አትሆንም አንተ….ነህ ..I hate …..” እያለ ጥሎት ይሄዳል።

በሁኔታው ግራ የተጋባው ልጅ እንደገና ይህንኑ ታሪክ ላባቱ ይወስድና አማራ ምንድነው? ብሎ ይጠይቃል። አባት ብዙ ዝርዝር ውስጥ ሊገባ አልፈለገም። “ ጓደኛ አልሆንህም ካለህ ምርጫውን አክብር። አትረብሸው። ሌላ ጊዜ በደንብ ስትተዋወቁ ጓደኛ ትሆናላችሁ “ በማለት ልጁን ያጽናናል።

ይህ ቡቃያ ከእናቱ ወይም ከአባቱ የዘር ፖለቲካ ልክፍተኛ እንዳለበት ምንም ጥርጥር የለውም። በዚህ መልኩ ነው የጥላቻ በሽታ ከቤተሰብ ወደ ልጆች የሚተላለፈው፤ የሚጋባው። አሁን በሀገራችን ስልጣኑን የተቆጣጠሩት የሕውሀት መሪዎች የዚህ አይነት አስተዳደግ ውጤቶች ናቸው ብየ ነው የማምነው። መልካሙ ነገር እነዚህ ህጻናት እኛ ካደግንበት ወይም ሀገርቤት ያሉት ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ከሚያድጉበት የተሻለ አለም ውስጥ ስለሆነያሉት፤ ነገ ጠዋት ሁላችንንም ወላጆችን እንደሚያርሙንና እንደሚተቹን የሚያጠራጥር ነገር የለውም፤ ምክንያቱም መንግስታቸው “በቆዳ ቀለምና በዘረኝነት አትታወር” እያለ ነውና የሚያሳድጋቸው።

በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ በወያኔ ዘረኛ ገዢ ቡድን አስተዳደር ስር ያሉት ሕጻናቶቻችን አየሩ ሁሉ በዘር ፖለቲካ ሰበካ፤ በጥላቻ ወሬ፤ በልዩነት ፕሮፓጋንዳ ጩኸት በተወረረበት፤ ንጹህ አየር ተንፍሰው ለማደግ ፋታ ባጡበት ሁኔታ ሬዲዮ፤ ቴሌቪዥን ወያኔያዊ ሀሰተኛ የውንጀላ ድራማና ወሬ ብቻ በሆነበት ዘመን፤በሀሰት፤ በክህደት የሀገርን ታሪክ፤ የህዝብን አንድነት የሚያረክስ ሴጣናዊ ወያኔያዊ የቁራ ጩኸት ብቻ በሆነበት ምድራችን ለሚያድጉት ህጻናቶቻችን የወደፊት እጣፈንታ መጨነቅ ያስፈልገናል።

ባለፉተ ሀያ አመታት ውስጥ በሀገሪቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምናየው አንዳንድ ምልክት ወያኔ የዘራው በሽታ የሚፈልገውን ፍሬ እያፈራለት መሆኑን ያመለክታል። በዘር ተለያይተው የሚደባደቡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ ለማየት ችለናል። ነገ ሀገሪቱን የሚረከቡ ዜጎች ናቸው። ወያኔ እያሳየን ያለው ምን ያህል ትውልዱን እያዘቀጠልን እንዳለ ነው። ተበልጠናል። ልጆቻችንን ለወያኔ የዘረኝነት ፕሮፓጋንዳ ሰለባ ከመሆን ልናድናቸው አልቻልንም። አንድ ሆነው እንዲቆሙ ወላጆች ማስተማር አልቻልንም። ከህብረተሰብም ከትምህርትቤትም በፊት ሰው የሚቀረጸው በቤት ውስጥ ነው። ኢትዮጵያዊ ማንነታቸውን፤ ህብር ህዝብነታቸውን፤ የባህል የቋንቋ የስነልቡና ውህደታቸውን አያት ቅድም አያቶቻው ከባእዳን ወራሪዎች ጋር ተፋልመው ያቆዩአት አንዲት የጋራ ሀገር እንዳለቻቸው፤ ባለመጠራጠር እንዲያውቁ አላደረግንም። ለዚህም ነው ከአንድነታቸው ይልቅ ልዩነታቸው እየጎላ የታያቸው ልጆች ወያኔ መፍጠር የቻለው።ለዚህም ነው የወያኔን ሴራና ተንኮል መረዳት አቅቶአቸው አንዲህ ተባልን እንዲህ ሆን ብለው ሆብለው ለጅምላ ድብድብ መፍጠን የቻሉ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ማየት የቻልነው።
ለራሳችንም የዘር በሽታ ልክፍተኛ የሆን ወገኖች በሽታችንን፤ ህመማችንን፤ዋጥ አድርገን ለልጆቻችን ደግደጉን መንገር አልቻልንም።

የኢትዮጵያ ልጆች እጣ ፈንታ በኛ በወላጆቻቸው ትከሻ ላይ ነው ያለው አንጂ በመርዘኛው የወያኔ ገዢ ቡድን እጅ ውስጥ አይደለም። ወያኔ እየጋታቸው ያለውን የመጥፊያ መርዝ እንዳይውጡ ማድረግ የኛ ፋንታ ነው። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ወላጅ በቤቱ ውስጥ የኢትዮጵያዊያንን እኩልነት ብዛትና አይነት ባህላችንን ቋንቋችንን አንድነታችንን የምድራችንን ልክ ማስተማር ይጠበቅብናል።

ከውጭ ወራሪ ጠላት የከፋ ጠላት ከውስጥ ስለተቆጣጠረን፤ በዘር በሽታ የተለከፍን ሁሉ አማራውም፤ ኦሮሞውም፤ ትገሬውም፤ አፋሩም፤ ሶማሌውም…ሁሉም!.... ካባቶቻችን የወረስነው የመጠላላት በሽታ ካለ ዋጥ አድርገን፤ ነገ አብረው መኖር ስላለባቸው ልጆቻችን፤ ቡቃዮቻችን እናስብ።

የሚቀጥሉት ሰላሳና አርባ አመታት ነገሩ ሁሉ አሁን አንዳለው ከቀጠለ፤ልጆቻችን እርስበርስ ሲናቸፉ፤ ወያኔና ከውጭ በገፍ እያስገቡአቸው ያሉት ባእዳን ባለሀብቶች ይህችን ሀገር ይቆጣጠሯታል። ይቀራመቷቷል። እነዚህ ከውጭ እያስገቡ መሬት የሚያድሏቸው ባእዳን ሁሉም ሀብታምና ትልልቅ መንግስታት ከጀርባ አላቸው። ቻይና፤ ሳውዲአረቢያ፤ አሜሪካ፤ እንግሊዝ፤ ሕንድ፤ወዘተ…ለህዝባቸው የተትረፈረፈ ምግብ፤ ለኢንዱስትሪአቸው ጥሬ ሀብት፤ ለሸቀጣቸው ማራገፊያ ሰፊ ገበያ ኢትዮጵያ እየተበለተችላቸው ነው።

መሬትን ለማረስ መጀመሪያ ደኑን መመንጠር እንደሚገባ መሬቱን ለባእዳኑ ለመሸጥ መጀመሪያ ወያኔ ዜጎቻችንን በመግደል እየመነጠረ የሚሸጠውን ቦታ እያመቻቸላቸው ነው። በቅርቡ የሱሬ ብሄረሰቦች መቶ ሀምሳ የሚሆኑ ከመሬታቸው ከቀያቸው ውስጥ ተሰብስበው በመትረየስ ተጨፍጭፈው ተጥለዋል። አሁን መሬቱ ተመንጥሯል። ባእዳኑ ገንዘቡን ከፍለው መረከብ ይችላሉ።የኢትዮጵያ ህዝብ ምን አይነት የማደንዘዣ መርፌ እንደወጉት አይታወቅም፤ ተራ በተራ እየገደሉ እስኪጨርሱት ተቀምጦ እየጠበቃቸው ነው።

ዛሬ እንዲጠላሉ አድርገን ያሳደግናቸው ልጆቻችን ነገ ምድራቸውን የተቀራመቷት ባእዳንና ወያኔዎች በሚያቀርቡላቸው ጠመንጃ ስራቸው መዋጋት ይሆናል። የምድሪቱን ቱሩፋትና በረከት በብዙ ሺህ ማይልስ ርቀት ላይ ያሉ ህዝቦች ይኖሩበታል። በብዙ ሺህ ማይልስ ርቀት ላይ የሚገኙ የሀብታም ልጆች ይፋፉበታል ያድጉበታል። ይህችው ምድር ያበቀለቻቸው ዜጎቿ ያልታደሉቱ፤ ይራቡባታል። እርስበርስ እየተታኮሱ ይገዳደሉባታል።በወያኔና መሬቱን በተሸለሙት ሀብታም መንግስታት ወታደሮች ይገደሉባታል።

ልጆቻችንን ከመጠላላት ፖለቲካ እናድን። ለማናችንም አይበጅም። እኛም በሽታው ካለብን ዋጥ አናድርገው። ቀጠሮ የምንሰጠው ጉዳይ አይደለም። ዛሬ!..ዛሬ!..ዛሬ ነው ጊዜው። ፍቅርና አንድነት ያለው ህዝብ ያሸንፋል።የጋራ ጠላታችን ወያኔን አምርረን እንዋጋ።እርስበርስ መጠላለፉ እልቂታችንን ያቀርበዋል።ለመዳን አንድ እንሁን!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Lkebede10@gmail.com

Monday, February 4, 2013

Ethiopia: ‘Judas of Wollayta’ shattered as pagan TPLF warlords cancelled his bizarre Sunday mass


The Horn Times breaking news, 3 Feb 2013.
by Getahune Bekele-South
Africa

Due to security concerns and the sectarian nature of Wollayta pastors, the TPLF has officially stopped the Sunday massweekly held at the grand palace and  those arrived today 3 Feb 2013,  including old as a hill self-made historian  Dr Lapeso Gedelebo are all turned away by federal police. The Ethiopian ruling minority junta instead appointed Tigray republic’s protestant high priest, Daniel Gebresilssie to conduct the service for one hour    with no outsiders allowed in except the immediate family members of PM Hailemariam Desalegn, unimpeachable sources told the Horn Times from Addis Ababa.
Since he moved to the official residence of the prime minister, Hailemariam Desalegn who claims to be an immaculate protestant Christian has been holding noisy and chaotic Sunday masses at the palace much to the irritation of his pagan masters, the TPLF warlords.
The deacons and deaconesses, the Netherlands ordained pastors-cum theologians and their prophetess wives from the emerging Wollyta bourgeoisie have been congregating every Sunday at the conspicuous palace, occupying it from Saturday night until the wee hours of Monday, some driving all the way from the rural town of Wollayta – Sodo, the birth place of  PM Hailemariam.
Nervously tolerated by Tigre palace guards and federal police commando units, the Wollyta crowd usually stays through the night reluctant to leave even after the 3pm scrumptious luncheon served by the first lady Roman Tesfaye, making the palace unavailable for state business.
According to our sources, the warning issued by palace authorities to the priestly Wollyta coterie to limit numbers of worshippers never been heeded but it was the attitude of the pastors that led to the total cancellation of the gathering.
On the pulpit decorated with TPLF flag and pictures of the dead tyrant Meles Zenawi, spurred on by the old curmudgeon Sibehat Nega’s anti-Amhara, anti Islam and anti Orthodox Church rhetoric, preacher after preacher prophesies the demise of Ethiopiawinet under the   “heavenly” rule of the puppet premier Hailemariam Desalegn.
Although such teachings were pleasing to the Tigre junta, Pastor Semaiat Toma Woldeselassie’s January 26 2013, vision of seeing the late Meles Zenawi walking in paradise with Jesus by his side was the most embarrassing appeasement which made the warlords blushed in shame while the first lady and the premier broke into song with the crowd shouting “halleluiah.”
“With all respect to protestant churches of Ethiopia, this one is of sectarian nature and their god is the dead colonizer Meles Zenawi. They are here to please their Tigre bosses and swear loyalty to the oppressive minority rule. They say unprintable things about other churches and religions in the name of prophesy.” Our source who requested anonymity said.
Nicknamed Judas of Wollyta by his own people, the prime minister has time and again showed that he is a man of very low intellect just like his murderous predecessor Meles Zenawi.
Reports are that Hailemariam is shattered by the decision to cancel the mass and from now, every Sunday, he has to spend an hour listening to the tiresome pedagogue Pastor Daniel as the warlords slowly taking control of all aspects of his life by isolating him from the people.
“It isn’t moral for a sitting prime minister to associate himself with a certain occult  powers and applaud them for hurling cheap insults on other churches and religions. Ethiopia is a secular state.” Our source added.
infohorntimes@gmail.com    


Saturday, February 2, 2013

The AU's love for dithering leaves the West in charge, again


By LEE MWITI | Wednesday, 


The last time the African Union held a pledge drive, only four African presidents showed up, including the host, then-Ethiopian prime minister Meles Zenawi.
The said fundraiser, for the Somali famine, had been much-delayed, despite fierce criticism of Africa’s own inertia over the unfolding humanitarian crisis with memories of the Ethiopian famine still fresh.
To make matters worse, the amounts pledged bordered on the pitiful, starting with the AU’s own paltry donation of $500,000 - against a budget of $1.5 billion.
This week, another fundraiser was held at the same venue, this time for Mali. This time round, the folks at the AU were brighter, pegging it to the just-ended heads of state summit to ensure a full house. Unexpectedly, the AU pledged what it itself agreed was an “unprecedented” $50 million towards stabilising the war-torn country.
Some $455 million—half of the target - was raised, again mainly by pledging. The identity of the biggest donors was interesting: Japan, still shell-shocked after losing ten of its citizens to the Algerian hostage crisis, will fork out $120 million; the US, clearly terrified of a new terrorism front, will give $96 million; and Germany $20 million.
Interestingly, China and India pledged only $1 million each. So much for the South-South co-operation.
But I digress.
At any AU heads of state summit the unstated theme is always of African sovereignty—the "African solution to the African problem" dogma. While already criticised as nothing more than a cloak to protect their hold on power, it has become even harder to defend in the wake of the Arab Spring.
Africa's decision-makers' love for twiddling their thumbs and sitting on their hands has been on full display, forcing the West to step in - the very idea that is anathema to many of these leaders.
For their African sovereignty ruse to even survive this decade, the leaders need to ditch the NGO-model of endless conferencing in plush hotels, which achieves very little on the ground.
'Total reconquest'



The assault on northern Mali was mooted last year as Islamists rapidly seized huge swathes of the country. The UN in keeping with its penchant for bureaucracy, needed former colonial power France to draw up an intervention plan. Even then, boots could only be on the ground in September, the clever people in New York said.
This should have been a golden chance for the AU, and more specifically West Africa through its Ecowas grouping, to seize the moment and chart a solution—political or military—for Mali.
Instead Ecowas and AU heads shuttled leisurely between capitals, while military chiefs from member countries were as late as last week still engrossed in planning meetings.
France had to swiftly step in as the militants begun an ominous advance south, threatening Bamako, the capital.
At the weekend’s summit, outgoing AU chairman Thomas Boni Yayi told assembled African leaders that their response to the conflict in Mali had been too slow. France's action was something "we should have done a long time ago to defend a member country,” he admitted.
But unfortunately AU lethargy is not an isolated event. While African leaders again dithered endlessly over what to do over Libya, NATO jets bombed Muammar Gaddafi out of power.
It again took the intervention of the French to eject Ivorian strongman Laurent Gbagbo from power, after he thumbed his nose at the popular will following an election he handily lost.
In the Democratic Republic of Congo, the mess in the east appears patently unresolvable because African countries are themselves accused of fanning the conflict. In neighbouring Central African Republic, foreign troops continue to provide a bulwark against rebels eager to oust President Francois Bozize from power.
It remains manifest that the West will always find a reason to intervene as long as African leaders lack spine and continue to shield each other's regimes from regional and international justice.
And with each intervention, a little bit more of the continent’s much-touted sovereignty, and pride, is chipped away. It was telling to hear France say that its goal in Mali is “total reconquest.”
Would anyone bet against the next round of neo-colonialism?

Monday, January 28, 2013

እናት ቤተ ክርስቲያናችን አልተከፈለችም


ጌታቸው ኃይሌ
መግቢያ፤

"ቤተ ክርስቲያናችን ከሁለት ተከፈለች" የሚል ሥጋትና ሐዘን ከብዙ አቅጣጫ ይሰማል። እውነት ተከፍላ ከሆነ ሥጋቱንና ሐዘኑ የሁላችንም ነው። ግን ለመሥራቿ ክብርና ምስጋና ይግባውና፥እና ቤተ ክርስቲያናችን አልተከፈለችም። ከፈሏት የምንላቸው ካህናትም፥ አለመከፈሏን ደጋግመው ተናግረውታል። ሳትከፈል ተከፈለች ማለት ያሳዝናል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንኳን ዛሬ፥ መከፋፈልን የሚያመጡ የነገረ መልኮት ብጥብጦች በተነሡባቸው የተለያዩ ዘመናት እንኳን፥ ጥቂት ተሞክሮ እንደሆነ ነው እንጂ፥ አልተከፈለችም። ስለዚህ መዓቱ እስኪያልፍ ድረስ፥ ቅዱስ ገብርኤል "ንቁም፡ በበህላዌነ፡" እንዳለው፥ ባለንበት ነቅተን እንጽና፤ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ነፃነት ተባብረን በአንድነት እንሥራ።
ቤተ ክርስቲያን መከፈል የሚደርስባት በነገረ መለኮት ላይ የተለያዩ ትርጒሞች ሲነሡና ስምምነት ሲጠፋ ነው። በእንደዚህ ያለ ጊዜ፥ ጉዳዩን በጉባኤ ለማየት የቤተ ክርስቲያን ባለሥልጣናትና ሊቃውንት ስብሰባ ያደርጋሉ። ስብሰባ "ጉባኤ" ወይም "ሲኖዶስ" ይባል ነበር። "ሲኖዶስ"
ማለት፥ "የሃይማኖትን ጉዳይ ለማየትና ለመወሰን የተሰበሰበ መንፈሳዊ ጉባኤ" ማለት ነው።
ሲኖዶሱ የቀረቡለት አስተያየቶች በሰፊው መርምሮ አንዱን ሲመርጥ ሁሉም ከተስማሙበት፥አለዚያም በዲሞክራሲ ሥርዓት በድምፅ ብልጫ ያለፈውን ሁሉም ከተቀበሉት፥ በቤተ ክርስቲያን መከፋፈል አይፈጠርም። ግን በዓለም-አቀፍ ደረጃ በተደረጉት ሲኖዶሶች ጊዜ የተፈጸመውን
ስናይ፥ ሁል ጊዜ ከሙሉ ስምምነት ላይ አልተደረሰም። በዚህም ምክንያት፥ ኒቅያ ላይአርዮሳውያን፥ ኤፌሶን ላይ ንስጥሮሳውያን፥ ኬልቄዶን ላይ መለካውያን (እነሱ "ተዋሕዶዎች"ወይ "ያዕቆባውያን" ይላሉ) ተለይተው የየራሳቸውን ቤተ ክርስቲያን አቋቁመዋል። "እንተ፡ላዕለ፡ ኲሉ፡ ጉባኤ፡ ዘሐዋርያት፡ (ከሁሉ በላይ የሆነች ሐዋርያት ያቋቋሟት ቤተ ክርስቲያን)
ተከፈለች፤ ተከፋፈለች። ከዚያ ወዲህ፥ ለጉዳይ ካልሆነ፥ አንዱ ከሌላው አይደርስም፤ የአንዱ ቤተ ክርስቲያን ምእመን ለማስቀደስ ከሌላው ቤተ ክርስቲያን አይሄድም።

በአንድ አካል ሁለት ራስ፤

የዛሬው ችግራችን ይኸ ዓይነት አይደለም። ማንም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምእመን ከማንኛውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሄዶ ማስቀደስ ይችላል። በስደት ላይ ያለነው ምእመናን ኢትዮጵያ ስንሄድ ከማንኛውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ሄደን ማስቀደስ እንችላለን። ከኢትዮጵያ የመጡም ከእኛ ጋር ያስቀድሳሉ። እዚያም እዚህም ያለነው አንድ የሃይማኖት ባህል ያለን አንድ ሕዝበ ክርስቲያን ነን። ችግራችን በአንድ ዘመን ሁለት ፓትርያርኮች መኖር ነው-- በአንድ አካል ላይ ሁለት እራስ።

ፓትርያርኮቹ አንዱ ኢትዮጵያ አንዱ አሜሪካ ሆነው፥ "ያንኛውን ትታችሁ እኔን ተከተሉስላሉን ግራ ተጋባን። ግማሾቻችን አንዱን፥ ግማሾቻሻችን ሌላውን ተከተልን፤ ሌሎቻችን ማንንም አልተከተልንም። ሆኖም፥ የአንዱ ፓትርያርክ ተከታይና የሌላው ፓትርያርክ ተከታይ ወይም ገለልተኛው የሃይማኖት ወንድማማቾችና እትማማቾች ናቸው። እንዲያውም ቤተክርስቲያን "ቤተ ክርስቲያን" የምትባለው ሕዝበ ክርስቲያኑን (ኤክሌሲያን) ለማመልከት ነው።
"ጉባኤ፡ ዘሐዋርያት፡" (የሐዋርያት ስብስብ) የተባለችውም ስለዚህ ነው።

ካህናቱ ከላይ እስከ ታች ልኡካን (ጸሎት በመምራትና ሃይማኖት በማስተማር ሕዝበ ክርስቲያኑን እንዲላላኩ የተላኩ) ናቸው። ቅዱስ ጳውሎስ፥ "ሁላችሁም የክርስቶስ ምእመናን ስለሆናችሁ፥እኔ የጳውሎስ ነኝ፤ እኔ የአጵሎስ ነኝ ማለታችሁን ትታችሁ በክርስቶስ አንድነታችሁን ጠብቁ ስላለን ከውዝግቡ ውስጥ በወገንተኝነት መግባትና ለውዝግቡ ሕይወት መስጠት የለብንም።ይህ ብቻ ሳይሆን፥ በመብታችን ተጠቅመን መፍትሔ መፈለግና ውዝግቡን ማብረድ ግዴታችን ነው። መፍትሔ ከተወዳዳሪዎቹ አይጠበቅም። ሆኖም፥ ያልተከፈለች አንድ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ፓትርያርክ ሊኖራት ስለማይገባ፥ አንዱን ብቻ እንከተላለን። ያንን ማድረግ የምንችለው፥ በስሜትና በምኞት ሳይሆን፥ የችግሩ መንሥኤ ግልጽ ሲሆንልን ነው።

የችግራችን መንሥኤ፤

ከዚህ አጣብቂኝ ያደረሰንን ምክንያት ሁሉም ቢያውቀውም፥ በአጋጣሚው እንደገና በአጭሩም ቢሆን ማንሣት ይገባል። ወያኔዎች የፖለቲካውን ሥልጣን እንደያዙ፥ ቤተ ክርስቲያኗንም ተቆጣጠሯት። መንበረ ፓትርያርኩን የያዘውን ርእሰ ቤተ ክርስቲያን (ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስን) ገፍተው የራሳቸውን ሰው (ዶክተር አባ ገብረ መድኅን ይባሉ የነበሩትን አስከድተው) አስቀመጡበት። በዚህም ሁለት ታላላቅ ብሔራዊና ታሪካዊ ወንጀል ፈጸሙ። (1)"ፓትርያርክ በሕይወት እያለ ሌላ ፓትርያርክ አይሾምም የሚለውን የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና ጣሱት፤ (2) በሀገሪቷ ላይ የዘሩትን ጎሰኝነት ዘረኝነት ከማታውቀው ቤተ ክርስቲያን አስገቡት።ኅብረተ ሰባችንን በዚህም በዚያም አፈረሱት፤ አፈራረሱት። ያልታመመውን ሁሉ በሽተኛ አደረጉት።

ወያኔዎች አሁንም ኢትዮጵያ ያሉትን ጳጳሳት በጥብቅ እንደሚቆጣጠሯቸው ለማንም ግልጽ ነው። እዚህ ሀገር የተቋቋመው ሲኖዶስ ጥር 9 ቀን፥ 2005 . . ባወጣው መግለጫ ላይ "ቀደም ሲል ለቀኖና ቤተ ክርስቲያን መፋለስ ምክንያት የሆነውና ቅዱስ ፓትርያርኩን በግፍ ከመንበራቸው ያሳደዳቸው ኃይል አሁንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነትና ክብር አለመፈለጉ ብቻ ሳይሆን፡ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማጥፋት ትውልድንም በመንፈሳዊ ሕይወቱ ለማዳከም ቆርጦ የተነሣ ኃይል . . . ነው" ብሎታል። በወያኔ አለንጋ የሚነዱትን ጳጳሳት እናዝንላቸዋለን እንጂ፥ አንፈርድባቸውም፤ ሁሉም ወዶ ገባ አይደሉም።

እንዲህ ከሆነ፥ ምእመናን ይኸንን ግፍና ጭቆና አንቀበልም። ቅዱስ ያዕቆብ ጋኔንን እምቢ በሉት እንዳለው፥ ለሃይማኖታችን፥ ለታሪካችን፥ ለማንነታችን ስንል፥ ያለማወላወል የጋኔንን ጭፍሮች እምቢ አሻፈርኝ እንላቸዋለን። አባቶች መነኮሳት፥ ከጸሎታቸው አንዱ "ለስምህ ሰማዕት የምንሆንበት አጋጣሚ ፍጠርልን" የሚል እንደነበረ፥ መነኲሴው ፓትርያርክም ወያኔ ሲገፋቸው፥ ሰማዕትነቱን ባይሸሹት ክብሩ ለቤተ ክርስቲያኗ፥ ለመንጋቸው፥ ከሁሉም ይልቅ፥ለራሳቸው ይሆን ነበር። ሆኖም፥ መንግሥት እጁን ከቤተ ክርስቲያን ላይ እንዲያነሣና ግፉዓን እንዲካሱ፥ ስዱዳን እንዲመለሱ፥ እስከ መጨረሻዋ እስትንፋሳችን እንታገላለን።

ሊሆን የሚገባው መፍትሔው፤

የተቃውሞ ዘዴያችን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማለት፥ በእኛ በምእመናኑ ላይ፥ የፈራነውን መከፋፈል የማያመጣብን መሆን አለበት። የአዲስ አበባው ፓትርያርክ ሲሞቱ ብዙዎች(የስደተኛው ፓትርያርክ ደጋፊዎች ሳይቀሩ) ችግሩ የፓትርያርክ ጉዳይ ወይም ወያኔዎች የሞቱ መስሏቸው፥ ቀና መፍትሔ ተጠባብቀው ነበር። እዚያም ሆነ እዚህ፥ ፓትርያርክ ሲሞት ፓትርያርክ ሊተካ እንደሚችል ልብ አላሉትም። ችግር የፈጠረብን የወያኔ ኀይል መሆኑንሁላችንም ካመንበት፥ መፍትሔው ያንን ኀይል ማስወገድ ብቻ ነው። የፓትርያርኩ ከመንበ ራቸው መመለስ የመፍትሔ ውጤት እንጂ መፍትሔ አይደለም። ዋናው መዘዝ የወያኔ እርኩስ እጅ ነው። ወያኔ ከሥልጣን ካልተወገደ፥ ወይም ፖሊሲውን ካልለወጠ፥ የተገፉትን ፓርትያርክ ከመንበራቸው መመለስ ብቻውን የችግሩ መፍትሔ አይሆንም።
ሕዝቡ "መንግሥት እጁን ከቤተ ክርስቲያን ላይ ያንሣ" እያለ ሲጮኽ፥ የውጪው ሲኖዶስ ጥረቱንና ትኲረቱን የተገፉትን ፓትርያርክ ከመንበራቸው እመመለስ ላይ ካደረገ፥ ዓላማውን ጠባብ የሥልጣን ሽኩቻ ያስመስልበታል። እስቲ እናስበው፤ መንግሥት ቤተ ክርስቲያንን በመቆጣጠር ላይ እያለ፥ ፓትርያርኩ ቢመለሱ፥ ጉዳቱ ለፓትርያርኩም ለታጋዩም የከፋ አይሆንምን? "እኔም እንደሌሎቹ ጳጳሳት የወያኔ ካድሬ ልሁን" ማለት እኮ ነው። ከገቡ፥ ወያኔ ሳይውል ሳያድር ካድሬው ያደርጋቸዋል። የኛም ትግል ይዳከማል። የሚዳከመው ፓትርያርክ ስለምናጣ ሳይሆን፥ ወያኔ ከመንበራቸው ላይ አስቀምጦ በስማቸው መግለጫ እያወጣ አፋችንን በዓለም ፊት ስለሚዘጋው ነው። መንበራቸውን ለማስለቀቅ የቻሉ የጋኔን ጭፍራዎች ከመንበራቸው ላይ አስቀምጠው ዝም ማሰኘት አይችሉም ብለን ተስፋ አናደርግም። የምንመለሰው ለመታገል ነው ካሉ፥ በድርድሩ ጊዜ በሩ ገርበብ ብሏል። ጠላትን ከዚህ የተሻለ የጦር ሜዳ አስተካክልልን አይሉትም።

ሲኖዶስ፤

ለአንድ ቤተ ክርስቲያን የሚኖራት አንድ ሲኖዶስ፥ አንድ አመራር ብቻ ነው። ይኸንን ሕግ ሁለት ሲኖዶስ የፈጠሩት፥ አዲስ አበባ ያሉት ካህናትና ስደተኞቹ ካህናት፥ ያውቁታል። ከኢትዮጵያ ውጪ ያለነው ሕዝበ ክርስቲያን፥ ካህናቱን ጨምሮ፥ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ስደተኞች ነን። የምናደርገው ትግል ሀገራችን ነፃ ሆና በነፃነት እንድንኖርባት ነው እንጂ፥ ይኸን ካላገኘን ብለን በተሰደድንበት ዓለም፥ ኢትዮጵያዊ መንግሥትና ኢትዮጵያዊት ቤተ ክርስቲያን
ልናቋቁም አይደለም። ስለዚህ፥ የተሰደዱትን ካህናት የምጠይቃቸው፥ "የእኛን ሲኖዶስ ተከተሉ" እያሉ ሕዝብ ማስጨነቃቸውንና የመከፋፈል ምክንያት መሆናቸውን ትተው፥ የድዮስጶራው ሕዝብ ወያኔን ሲቃወም ተጨማሪ ኀይል እንዲሆኑ ነው። "የእኛን ሲኖዶስ ተከተሉ" ማለት የሃይማኖት ስደተኞች ሳንሆን፥ የሃይማኖት ስደተኞች ሁኑ፤ ከኢትዮጵያው ሕዝበ ክርስቲያን ተለዩ" ማለት ነው። ብዙዎች የሚከተሏችሁ ወያኔ የተጠቃላቸው መስሏቸው፥ ቢቸግራቸው ነው እንጂ፥ ኢትዮጵያ ካለው ሕዝበ ክርስቲያን መለየት ፈልጎ አይደለም። የአንድ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ማእከል ከሕዝቡ ማእከል መሆን እንዳለበት መካድ አይቻልም። ስለዚህ፥ በሕዝብ ማህል ያለውን የኢትዮጵያውን ጭቁን ሲኖዶስና የቤተ ክርስቲያንን አመራር ታግሎ፥ ከወያኔ እጅ ነፃ አውጥቶ፥ ከመውሰድ ይልቅ፥ ከኢትዮጵያ ውጪ ሌላ ሲኖዶስ ማቋቋም ሕጋዊ አለመሆኑን ሲኖዶስ አቋቋሚዎች ያውቁታል። መፍትሔ አድርገው ያዩት፥ የኢትዮጵያውን ሲኖዶስ "ሕገ ወጥ" እነሱ ያቋቋሙትን "ሕጋዊ" ማለት ነው። ግን ሁለቱም ሕገ ወጥ ናቸው። ልዩነቱ የኢትዮጵያው ሲኖዶስ "ሕገ ወጥ" የሆነው መንግሥት አስገድዶት ሲሆን፥ የውጪዎቹ ካህናት ሲኖዶስ ያቋቋሙት በስደተኛው ሕዝብ ብዛትና ብሶት በመጠቀም ነው። በወያኔ ጭቆና የተሰደደው ሕዝብ ብዙ ባይሆን፥ ስዱዳን ጳጳሳት ምንም ብዙ ቢሆኑ ብቻቸውንሲኖዶስ አያቋቁሙም ነበር።

በሲኖዶስ ስም የተደራጁት ለአገልግሎት እንዲመቻቸው ብቻ ከሆነ፥ ሕገ ወጥ ሲኖዶስ ሳያቋቁሙ የሚፈለገውን አገልግሎት መስጠትና ሕዝበ ክርስቲያኑን አስተባብሮ የወያኔን ክንድ መመከት ይቻላል። ሕገ ወጥ ሲኖዶስ ማቋቋም ግን፥ ሕዝብ ስለሚከፋፍል መንበሩን ከመልቀቅ የከፋ ሌላ ጥፋት መጨመር ነው።

የድዮስጶራው መንፈሳዊ ችግር፤

የድዮስጶራው ሕዝበ ክርስቲያ የሚኖረው ኢትዮጵያ ካለው ሕዝበ ክርስቲያን የተለየ ችግር በሚያስከትል በተለየ የባህል አካባቢ ነው። ይኸ ልዩ የባህል አካባቢ የሚያመጣውን ችግር የሚረዱለት ካህናት ያስፈልጉታል። ስለዚህ፥ የድዮስጶራው ካህናት ድርጅት አቋቁመው፥ የሕዝቡን ችግር ለመረዳትና መፍትሔ ለመፈለግ በየጊዜው እየተሰበሰቡ መመካከር፥ እርስ
በርሳቸው መማማር፥ ልምድ ካላቸው አብያተ ክርስቲያናት ተናጋሪ እየጋበዙ ልምዱን እንዲያካፍላቸው መጠየቅ ያስፈልጋቸዋል። ያንን ድርጅት "መካናዊ (ሀገረ ስብከታዊሲኖዶስ" ወይም "ረክበ ካህናት ጉባኤ" ሊሉት ይችላሉ። ቀኖና ነው። የሚከፋፍለንን ሲኖዶስ በዚህ በሚያስተባብረን ሲኖዶስ ስም ቢጠሩት፥ ያስከብራቸዋል። ሁላችንም እንከተላቸውና፥"ከፋፋይ " የሚለው አስከፊ ታሪካቸው ይፋቅላቸዋል።

ኑዛዜ፤

ስደተኞቹ ጳጳሳት (አባ ይስሐቅ፥ አባ መልከጼደቅ፥ አባ ዜና ማርቆስ፥ አባ ኤልያስ) አንድ ጊዜ፥ ኒው ዮርክ ከተማ ስብሰባ አድርገው በማግስቱ፥ ሲኖዶስ ማቋቋማቸውን ለቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ለተሰበሰብነው ነገሩን። በዚህ ጊዜ፥ "ጥቂቶች ብዙዎችን አይወክሉም፤ ይኸ እንዴት ይሆናልበሚገባ አስባችሁበታልን? " የሚል ጥያቄ ሳነሣ፥ ዶክተር በላቸው ዓሥራት ፖለቲካዊ ጥቅሙን ካስረዳ በኋላ፥ አባ ገብረ ሥላሴ ተነሥተው፥ "በወያኔ ስር ያሉት ጳጳሳትም ከእኛ ጋር ናቸው"
አሉ። ይህን ሲኖዶስ ኢትዮጵያ ያሉት ጳጳሳት ከደገፉት፥ ወያኔን የሚያጠቃ ኃይል ካለው በማለት ደግፌው ነበር። አሁን ሳየው አንዱንም ተስፋ አልፈጸመልንም። እንዲያውም፥ ገደል የሚያገባ መንገድ ይዞ መጓዝ ስለሆነ እንመለስ።