Tuesday, November 20, 2012

The opportunists

'ርግጥ ወያኔዎች ልቦና ገዝተው፣ ህሊናቸውን ፈትሸውና ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን እስከአሁን ማጥፋት እንዳልቻሉ አገናዝበው፤ የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ በመጠየቅ፣ሁሉን አቀፍ ለሆነ ዲሞክራሲያዊ ሽግግር ራሳቸውን ቢያዘጋጁ፤ ለሀገሩ ቅን የሚያስብ ሁሉ ደስታውን ባልቻለው ነበር። ደግሞም ማድረግ ካለባቸው ዛሬ ሳይሆን ትላንት ነበር፤ ትላንትም ባይሆን ዛሬ ነበር። አዎ....ትላንትም ዛሬም አላደረጉትም። የማንነት ባህሪያቸውና አላማቸው አይፈቅድላቸውምና።
ስለዚህም ተወደደም ተጠላ ወያኔን ለማስወገድ አስግዳጅ ሀይል መፈጠር  ግድ ይሉዋል
የሀገር ውስጥ ተቃዋሚዎችም ከፍርሀት ቆፈናችሁ ተላቃችሁ ለህዝብና ለሀገራችሁ ማንነታችሁን የምታሳዮበት ግዜ አሁን ነው። የትግሉ መነሻም ሆነ መድረሻ ለኢትዮጵያናዊያን በኢትዮጵያዊያን እስከ ሆነ ድረስ እንዳለፈው ግዜ "የከክልኝ-ልከክልህ" አይነት ቅንጅት/ካውንስል/'ባር ሳይሆን፤ ለህዝብ ግልጽ የሆነና እውነተኛ ዲሞክራሲ፣ እውነትኛ አንድነትና ህብረት መፈጠር አለበት። ሀገርንና ትውልድን የማትረፍ ጥያቄ፤ ከወሬ፣ ከወረቀትና ከኢተርኔት ከፌስቡክ መፈክር አልፎ፣ እውነቱን በማውጣት፣ ራስን በመፈተሽ፣ ካለፈው በመማርና 'ራስን ለክቡር አላማ ለመሰዋአትነት በማዘጋጀት፤…… 1ኛ/ ተግባር! 2ኛ/ ተግባር! 3ኛ/ ተግባር!.... ከሁላችንም  ይጠበቃል። 

Friday, November 16, 2012

Genocide and Ethnic Cleansing


Genocide: The deliberate and systematic destruction of a racial, political, or cultural group.

Ethnic Cleansing: The elimination of an unwanted group from a society, as by genocide or forced migration.


Any discussion of genocide or ethnic cleansing would seem to be straightforward, both in the subject matter itself and in the myriad examples one could bring to mind. As these topics are studied in greater depth, however, the discussion invariably becomes far more complicated. Defined as "the deliberate and systematic destruction of a racial, political, or cultural group," genocide tends to evoke thoughts of the Holocaust of World War Two--the most egregious and infamous example of the mass killing of people based on their ethnic or religious background. For many people, that is the full extent of what genocide means. Today, however, the word genocide draws upon an even more complex body of history and scholarship, focusing on the motivation of the perpetrators. By narrow definition, genocide can only occur when there is a deliberate attempt to completely destroy all members of a particular group. As such, there are few clearly identifiable examples of genocide.
The phrase "ethnic cleansing" may embody just the opposite. Ethnic cleansing has been defined as "the elimination of an unwanted group from society, as by genocide or forced migration." This definition is inherently broader than that of genocide alone, and thereby encompasses mass killings and forced removals in far greater number and scope. The U.S. State Department, in a recent report on Kosovo, concluded that ethnic cleansing "generally entails the systematic and forced removal of members of an ethnic group from their communities to change the ethnic composition of a region." The latter definition, while accurate for that particular situation, is seemingly too narrow to be a useful descriptor of a majority of situations which are encompassed in the broader definition. Ethnic cleansing, then, may involve death or displacement, or any combination thereof, where a population is identified for removal from an area.
By using the above definitions, most mass killings and forced relocations fit into one or both of the two discrete categories that are presented. Acts of genocide, as the more narrowly defined term, have been recognized by the United Nations nine times this century. These examples include the purge of Armenians by the Turks beginning in 1915, Jews killed in the Ukraine in the late 1910's as well as during the Nazi regime, Cambodians under the Khmer Rouge in the 1970's, Bosnian Muslims in the former Yugoslavia early this decade, and the slaughter of the Tutsi minority by the Hutu majority in Rwanda in 1994. At least ten additional examples of ethnic cleansing were not recognized by the U.N., due to the criteria used to determine what qualifies as genocide. While genocide is globally recognized as a crime against humanity, ethnic cleansing is not. It is unlikely that such a broad and oft used term could garner the support to declare ethnic cleansing, as a whole, as a crime against humanity.
The United Nations was the forum in which genocide was declared to be a crime under international law--either in times of war or peace. The term had already been coined by Raphael Lemkin, a Polish-born advisor to the then U.S. War Ministry, in a book he published in 1944. Lemkin was the first to argue that genocide is not a war crime, but a crime against humanity-- something uniquely different from anything that had been seen before.
The formal definition came in the 1948 Convention for the Prevention and the Punishment of the Crime of Genocide. Genocide is defined in the Convention as any of the following acts committed with intent to destroy, in whole or in part, a national, ethnic, racial or religious group, as such: a) killing members of the group; b) causing serious bodily or mental harm to members of the group; c) deliberately inflicting on the group conditions of life calculated to bring about its physical destruction in whole or in part; d) imposing measures intended to prevent births within the group; e) forcibly transferring children of the group to another group. In the years since the Convention came into force, reconsideration of its points has led to the addition of acts of genocide occurring prior to World War Two.
Both "genocide" and "ethnic cleansing"--as words and concepts--have drawn criticism. Some critics suggest that genocide is a word used too frequently and too loosely in our vernacular. Alain Destexhe, former Secretary General of MÇdecins Sans Frontiäres (Doctors Without Borders) at the time of the Rwandan conflict earlier this decade, argues that there are only three examples of genocide in the 20th century: Armenians killed by the Turks; extermination of Jews, Gypsies, and homosexuals by during World War II; and slaughter of the Tutsi minority by the Hutu majority in Rwanda in 1994. Destexhe fears that the ubiquitous use of the word genocide to describe any massacre or repressive situation is causing "genocide" to lose its vital meaning as a crime above all others, distinguishable by the single-minded intent behind the barbaric actions. While Destexhe worries that the meaning of the word will be diluted, other critics hope that their revisionist history will be aided by the too common usage of genocide. Particularly for those who do not believe that the Holocaust occurred, the overuse of "genocide" bolsters their propaganda that the Nazi extermination camps and the "final solution" were not really such a uniquely horrible period in history.
"Ethnic cleansing" has also been used to describe a group of people of similar nationality, race, or religion who are experiencing any kind of action which they consider objectionable. Illegal Jewish settlers in the Palestinian controlled territory of Israel believe themselves to be victims of ethnic cleansing when their own government decides to evacuate them in the name of preserving peace. Some people feel they are forced from their home countries because of prejudices that make their lives difficult or intolerable, though they may not actually fear for their physical safety. These examples demonstrate the difficulty in relying on the phrase "ethnic cleansing" to be self-explanatory. The given definition of ethnic cleansing might encompass these situations, but at the same time, may also diminish the seriousness often entailed in the use of the phrase.
The phrase ethnic cleansing has been drawn into the discussion often this decade, as examples of mass killings of persons with a distinctive commonality have abounded. In the former Yugoslavia a variety of groups-- Bosnians, Serbs, Muslims, and Kosovars--have fallen victim to relatively, and perhaps specifically, organized campaigns of ethnic cleansing in this decade alone. More recently we have seen a wave of violence in East Timor, which may yet be described as ethnic cleansing when more complete information becomes available. Both historically and in the present day, there are countless examples of genocide and ethnic cleansing around the world. With no shortage of instances of death and destruction wrought upon those who suddenly find themselves of the wrong ethnicity, religion, nationality or political belief, the time appears ripe for a reconsideration of the instrument which was to have brought such cases to a halt more than a half century ago.
In December of 1998, Secretary-General Kofi Annan spoke on the occasion of the 50th anniversary of the Genocide Convention. He recalled that with the adoption of the Convention, nations had bound themselves legally to forestall those who would perpetrate such actions wherever they might occur. He also noted that shamefully little was done to arrest these actions in progress, and only in their aftermath was significant action taken. The Secretary-General himself was accused, in the as yet unresolved circumstances of the Great Lakes region, of allowing genocide to proceed unhindered inside Rwanda in the spring of 1994. Mr. Annan was the designated head of peacekeeping operations for the UN at that time, and was apparently warned that Hutus were massing arms that could only be used to slaughter others. Despite his privileged knowledge, Mr. Annan did not request additional troops for the existing peacekeeping mission, nor seek to have the existing mission mandate altered to allow for confiscation of said weapons. Having been in a position to halt the imminent slaughter of half a million civilians, Mr. Annan as a high ranking and appropriately placed member of the UN bureaucracy had chose inaction. Additionally, some governments also refused to identify the situation for what it was--genocide in progress--in order to avoid their obligation to intervene under the Convention.
Rwanda is a more definitive example of genocide than most situations. While the lack of concerted international reaction there is inexplicable, it is certainly not the only example of turning a blind eye to the slaughter. Two million Cambodians were killed in the 1970's in what came to be considered genocide, albeit well after the fact. In very recent memory was the indiscriminate killing of Kurds in northern Iraq at the hands of Saddam Hussein. While not genocide by technical definition, this group was targeted because they threatened--more psychologically than physically or militarily--the totalitarian power and authority of Hussein. And there is no end in sight for this type of violence that is targeted against specific groups of people.
The General Assembly also reaffirmed the importance and necessity of the Genocide Convention in December of 1998, adopting resolution A/53/L.47, which expresses the concern of the body that many thousands of innocent human beings continue to be victims of genocide. Despite this action, and having a Convention which abhors these aforementioned circumstances, the parties to that instrument seem unwilling to abide by their word and fight against genocide. Some parties may fear the political ramifications of doing so, while others may be concerned about the specificity of the Convention's language in relation to the real world situations it is meant to contain. Cries of racism have even been heard from those who believe that decisions to intervene are based primarily on the skin colour of those being massacred and those responsible for the massacre.
The reality is that despite the stated desire among parties to the Genocide Convention fifty years ago to ensure that genocide would never again occur, the will to achieve that most important goal has been severely lacking. The strongest efforts have been aimed at punishing those who are responsible for genocide, primarily through individual criminal tribunals organized for that specific purpose. Even these endeavours--in Rwanda and the former Yugoslavia--have come about only in this decade. Those responsible for recognized acts of genocide over the last three decades have gone unpunished, despite demands from survivor and witnesses.
In recent years, such pressure has culminated in an extraordinary amount of effort to conclude the legal instrument, known as the Rome Statute, which may eventually lead to the establishment of a permanent International Criminal Court (ICC). The ICC would have jurisdiction over four classes of crimes, including genocide and crimes against humanity. The definition of crimes against humanity included in the statute is broad enough to include some of the currently unprosecutable offences now referred to as ethnic cleansing. Unlike the current ad hoc tribunals, which must be approved by the Security Council, there will be no veto power over the ICC. When 60 states have ratified the statute the court will come into operation. The lack of veto power will likely make the ICC a more effective international legal body than any previously conceived. Major nations have expressed reservations over the statute and may not be willing to ratify it.
The creation of the ICC seems a step forward in global efforts to halt the proliferation of mass killings and other egregious violence. This pattern has been recurring throughout this century, and despite rhetoric to the contrary, little serious effort has gone into abating these tragedies. Clearly, past attempts have not been successful, and the reasons behind that remain unclear. What must future efforts entail in order to successfully avoid this scourge? How many more people will have to die at the hands of their neighbours and countrymen before the human considerations outweigh the political ramifications? What will be required to finally end what should have been but a memory at the dawn of the 21st century?

by Karyn Becker

Questions
1) Should the definitions of genocide and ethnic cleansing be reviewed to allow for greater inclusiveness of those actions described as crimes against humanity?
2) Should the Convention be reconsidered for revision, including possible expansion to include cases of ethnic cleansing and mass killing that might not be included in a strict (Destexheian) interpretation of "genocide?"
3) Under what basic circumstances should the United Nations intervene in a situation of ethnic cleansing or genocide, or seek to have regional organizations do the same?
4) Will the International Criminal Court be an effective remedy to the continuing problem of genocide and ethnic cleansing?
Sources
Annan, Kofi. Press release on the Occasion of the fiftieth Anniversary of the 1948 Convention on the Prevention and Punishment of the Crime of Genocide. SG/SM/6822, December 8, 1999.
Bell-Fialkoff, Andrew. "A Brief History of Ethnic Cleansing," Foreign Affairs; summer 1993, pp. 110-121.
Destexhe, Alain. Rwanda and Genocide in the Twentieth Century. New York University Press, 1995.
www.uen.org/utahlink/lp_res/AnneFrankGenocide.html
UN High Commissioner for Human Rights. Convention on the Prevention and Punishment of the Crime of Genocide. www.unhchr.ch/html/menu3/b/ p_genoci.htm 
www.un.org --general search under the topics "genocide" and "ethnic cleansing."
www.un.org/icc --home website of the International Criminal Court.

Monday, November 12, 2012

መቻቻል ምንድነው?


ብዙ አንገብጋቢ የሆኑ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች አሉ፡፡ የቱን ጥለን የቱን እንደምናነሳ ራሱ ይቸገራል፡፡ ወዲህ ስንል በፖለቲካው መድረክ የዴሞክራሲው አፈናና እመቃ ገዝፎ ይታያል ብቻ ሳይሆን የማፊያው ሥርዓት - አልባ የወያኔ ሥርዓት መፈናፈኛ አሳጥቶን ይገኛል፡፡ ወዲያ ስንል የኑሮ ውድነቱ ከጥቂት ዘመነኞችና አጭበርባሪ ተውሳኮች በስተቀር አብዛኞቻችንን በቁማችን ገድሎ ቀብሮናል፡፡ እንዲያ ወዲያ ስንል ደግሞ በቂ የእህል ምርት ያለመኖር፣ ሥራ አጥነት እንዲሁም በዬጊዜው በአስደንጋጭ ሁኔታ እየጨመረ በሚሄድ የሕዝብ ብዛት ምክንያት እየተባባሰ የመጣው የምግብ ዕጥረት እያስከተለው ያለው ርሀብ በቀላል ሊድኑ ከሚችሉ በሽታዎች ሳይቀር እየተባበረ ሕዝብን እየፈጀ ነው፡፡ በጥቅሉ እንደ አንድ ማኅበረሰብ በመኖርና ባለመኖር አስቸጋሪ ምርጫዎች ውስጥ ተቀርቅረን የአንድዬን መልስ ብቻ እየተጠባበቅን እንገኛለን፡፡ ከሁሉም በባሰ ደግሞ በሃይማኖት ሰበብ የገባብን ችግር የተግዳሮቶቻችንን ጡዘት በብዙ እርከን ከፍ አድርጎት ባልጠፋ ችግር አላስፈላጊ መሰናክል እየፈጠርን አንዳችን አንዳችንን የጎሪጥ በማየትነገ ደግሞ ምን ይፈጠር ይሆን?› በሚል ሥጋት ተወጥረን እንደነገሩ ይመሻል ይነጋል፡፡ በመሀሉ ግን ለዚህ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ውጥንቅጡ የወጣ ቀውስ የዳረጉን የውስጥ ምንደኞችና የውጪ ጌቶቻቸው በኛ የማያባራ ሥቃይ እየተዝናኑ ለነሱ የተመደበው መከራ እስኪደርስ ለጊዜው በሰው ደምና ወዝ በተፈጠረ ሀብት በመዘፈቅ በፈንጠዝያና በደስታ ይኖራሉ፡፡

ጆሮ የማይሰማው የለም፡፡ በቀደምለት 97 የወያኔ ዳግማዊ ቀይ ሽብር ለማጣራት በወያኔው መንግሥት ተቋቁሞ በነበረው ኮሚሽን ከነበሩት 10 አባላት የሁለቱን አቋምና የመንግሥት ወገንተኝነት በኢሣት ቴሌቪዥን ተከታተልኩ፡፡ እነዚህ የታሪክ ጉድፎችሼህኤሊያስናዶክተርመኮንን ዲልጋሳ የሚባሉት ናቸው፡፡ የነዚህሰዎችየሃሳብ ልዩነት መሠረት መንግሥት በወቅቱ ሕገ መንግሥቱን ጎዳና ነውጠኞችለመከላከል ባደረገው ጥረት የተጠቀመው ኃይል በእጅጉ ተመጣጣኝ እንደሆነና እንዲያውም እንደሼካው ከሆነ ተቃዋሚዎች 16 ሺህ ሰው መስዋዕትነት መንግሥትን እንገለብጣለን በማለታቸውና የሞተው ሰው ቁጥር አንድ ሺህ እንኳን ባለመሙላቱ ከተመጣጣኝም በታች መሆኑን ገልጸዋል - እንደሳቸው እሳቤ መንግሥት ዜጎችን በመጨፍጨፍ ረገድ ገና ሊያወራርደው የሚገባው 97. የሚወራረስ ቀሪ ሒሳብ አለው የሚሉ ይመስላል፡፡ እነዚህሰዎችእንደሰውም እንደሀገር ዜግነትም እንደመሬታዊ ነዋሪነትም በጣም ያሳፍራሉ፡፡ በጊዜው እዚህችው ሀገር ውስጥ አብረን ስለነበርን ያን የመሰለ የተቃዋሚዎች 10 እና 16 ሺህ ሰው የደም ግብር እሳቤ ሼካው ከየት እንዳገኙት አላወቅሁም፤ በወቅቱም ይህን መሰል ነገር ከማንም አልሰማሁም፡፡ ይህን መሰል ነገር ቢናገሩ ልሰማ እችል እንደነበር እገምታለሁ፡፡ ግን ሼሁ የአላህ ሰው ሳይሆኑ በግድያና በጭፍጨፋ የሚደሰተውና ካለነዚህም የማይኖረው የሸይጣን ልዑክ ስለሚመስሉኝ ከወያኔው በልጠው ወያኔን ሆነው ማየታችን ብዙም ሊያስደንቅን አይችልም፡፡ በዚያ ላይ እንደሰማሁት የዘር ጉዳይም እየሳባቸው ሃይማኖታቸውን ያስከዳቸው መስሎኛል፡፡ እንጂ እርግጠኛ ነኝ በእስልምና ሃይማኖት ውስጥ መብቱን የጠየቀን ዜጋ እንደዐይጥ ጨፍጭፍ የሚል ጥቅስ አይኖርም፡፡

በዚያ ኮሚሽን ውስጥ ሰብሳቢውን አቶ ፍሬሕይወትን ጨምሮ ስምንቱ ዕንቁ ዜጎች እውነትን አከበሯት፤ ለሥጋቸው ሳይሳሱ ለማተባቸው አድረውና ለወጡበት ሕዝብ ወግነው ነፍሳቸውን በፈጣሪ ዘንድ ትልቁን ቦታ አስሰጡ፡፡ ኤሊያስ የተባሉት ለሥጋቸው ያደሉ ሃይማኖተኛ ነኝ የሚሉ ሰው ግን በሰው ሃይማኖት እያላገጡ ቀላልነታቸውንና ግብዝነታቸውን በኩራት አጋለጡ፤ እንደዚያ በትዕቢት እየተወጣጠሩ የሰውን ሃይማኖት ለማሽሟጠጥ መሞከሩ ግን አለማወቅን እንጂ ብልህነትን አያመለክትም፡፡ ደግሞም በዘወርዋራም ይሁን በቀጥታ መንገድ ኢየሱስ(ዒሣ) ላይ የማሸሞር የሞራል ብቃት ያላቸው አይመስለኝም፡፡ ከእዳሪ በማያልፍ አንድ እንጀራና ከመሬት በማያልፍ የዘረኝነት ልክፍት የተሸነፉት የዚህ ሰው ስም በታሪክ ዐምድ በጥቁር ቀለም ተጻፈ፡፡ ያሳዝናል፡፡በኔ ሃይማኖትግራህን ሲመቱህ ቀኝህን አዙርለትየሚል ነገር የለም፡፡ በዚህ እኔ አላምንም…” እያሉ ሰይጣናዊ ጥቅሳቸውን ሲደረድሩ እኔ አዘውትሬ በምከታተለው የእስላማዊ ‘Peace TV’ በስብከቱ ከልብ የምወደው የዶክተር ናይክ ዛኪር ሃይማኖታዊ የመቻቻል ስብከትና አስተምህሮ በአእምሮየ ብልጭ አለብኝ፡፡ እኙህ ሰው ከጀሃነም እንጂ ከእስላማዊ ልሂቃን መንደር እንዳልመጡም ወዲያውኑ አመንኩ፡፡ አንድ የሃይማኖት አባት እንዲህ ያለ ንግግር በፍጹም አይናገርም - ሼህ ኤሊያስንና እሳቸውን መሰል የነፍስንና የሥጋን መንገድ ለይቶ የማያውቅ ካልሆነ በስተቀር፡፡ የኢጣሊያንን የቅኝ ገዢ ወታደር ባርከውና ቀድሰው ወደኢትዮጵያ የላኩት የሮማው (ሊቀ?) ጳጳስ ትዝ አሉኝ፡፡ በየሃይማኖቱ እኚህን መሰል ማፈሪያ ሰዎች መኖራቸውን ሳስብ በሃይማኖት ካባ ውስጥ የሚሠራው ወንጀልና ደባ ቁልጭ ብሎ ታየኝ፡፡ ምን ይሻለን ይሆን? ለጊዜው እኔ እንጃ!እያደር ግን ሁሉም እየጠራ ይሄድና እያንዳንዳችን የየመክሊታችንን እንደምናገኝ ጥርጥር የለውም፡

በኢትዮጵያ እንደሚታየው ያለ የሃይማኖቶች በተለይም የክርስትናና እስልምና እምነት ተከታዮች ተሳስቦና ተፈቃቅዶ መኖር የትም የለም ቢባል ማጋነን አይደለም፡፡ በዚህን የመሰለ የጋራ ኅላዌ ላይ ይህን የኤሊያስን የመሰለ ቆርፋዳ ንግግር መቸለስ ምን ዓይነት ቅሬታን ሊፈጥር እንደሚችል መገመት አይከብድም፡፡ ለራሳቸው የማያውቁ ገልቱ ግለሰብ ሆነው ሳሉ በፍቅርና በመተሳሰብ በሚኖሩ የሃይማኖት ተቋማት ላይ ሊዘሩት የተነሱትው ወያኔያዊ የጠብ ዘር ግን ሊታረም ይገባዋልና ሌሎቻችን ከኚህ በቁም የሞቱ ሰው ንግግር ተነስተን ልንማር የሚቻለንን ቁም ነገር እንማር፡፡ መማር ደግሞዕድሜም ሆነ የሃይማኖት ድንበር አይገድቡትም፡፡

ከስሙ ብንነሳ የተማሩቱ እንደሚነግሩን እስላም ማለት ሰላም ማለት ነው፡፡ ሰላም ማለት ደግሞ ለፍቅር ሲባል ሁለት ወገኖች ልዩነቶቻቸውን በመተው መሀል ድረስ በመምጣት የሚተቃቀፉበት እንጂ አንደኛው አንድ ጠርዝ ላይ ቆሞ ሌላኛው መጥቶ እንዲያቅፈው የሚጠብቅበት የትምክህት ዐውድ አይደለም፡፡ የሚሰበከውና በተግባር የሚገለጠው እስካልተለያየ ድረስ በእስልምናም ሆነ በክርስትና ተቻችሎ መኖር ዋነኛው የሕይወት ምሰሶ እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ነብዩ መሀመድ(..) በሀገራቸው ተከታዮቻቸው ሲገደሉና ሲሰቃዩ፣ ሰውን አክባሪ እንግዳን ተቀባይ የክርስቲያኖች ንጉሥ የሆነ በኢትዮጵያ መኖሩን ገልጸው ወደዚያች ሀገር እንዲሄዱ፣ ካልነኳቸውም እንዳይነኳቸው በጥብቅ አስጠንቅቀው ነበር ወደዚች ቅድስት ሀገር እንዲሰደዱ የመከሯቸው፡፡ ይሄ በታሪክ ተመዝግቦ ያለ ነገር ነው፡፡ ዛሬ ዓለም ዘወርዋራ ናትና አሁን በምንገኝበት ውሉ የጠፋበት አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ብንሆንም የጥንቱ ሊረሳ አይገባም፡፡ የሀገራችን መመሪያ ደግሞሀገር የጋራ ሃይማኖት የግልበመሆኑ የፈለጉትን ሃይማኖት እየተከተሉ መኖር ያልተከለከለ ብቻ ሳይሆን የተፈቀደም መብት ስለሆነ ከዚያ ማፈንገጥ ተገቢ አይደለም፡፡ የሌለ ችግርን እየፈጠሩ በሃይማኖት ሰበብ ምድርን ጦር አምጪ ማለት ደግሞ አይገባም፤ ፈጣሪም የለመኑትን የማይነሣ የነገሩትንም የማይረሣ ነውና ይህ ዓይነቱ ቅብጠት ቢቀርብን የተሻለ ነው፡፡ ዘመናችን 21 መቶ ክፍለ ዘመን የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ምጥቀት እየተመዘገበበት ያለ እንጂ የመካከለኛው መቶ ክፍለ ዘመን የክሩሴድና የጂሃድ ዘመነ ድንቁርና ባለመሆኑ ሁላችን በፍቅርና በውዴታ ተስማምተን መኖሩ ነው የሚያዋጣን፡፡ የፉክክር ደጃፍ ሊኖር አይገባም - ሳይዘጋ ማደሩ ለሁላችን ስለማይበጅ፤ ተባብረን በሮችንና ብርድ ወይም ንፋስ የሚገባባቸው ቀዳዳዎችን ሁላችን እየተሸቀዳደምን በፍቅር ስለፍቅር መዝጋት ይኖርብናል፡፡ እልህና ባለፈ ታሪክ ላይ የተመሠረተ ብቀላና የቂም ቋጠሮ ደግሞ አንዱን ወገን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ይጎዳል፡፡ ያላጠፋን ወገን መበቀልሞ ላም ባልዋለበት ዓይነት ስለሆነ ከጅምሩ ሊታሰብም አይገባም፡፡ የየትኛውም ጠርዝ የለቀቀ አመለካከት ሰለባዎች ብንሆን ተጎጂዎቹ እኛና ቀጣዩ ትውልዳችን ብቻ   ነን፡፡

በአማርኛ አንድ ጥሩ አባባል አለ፡፡ያንቺ ልጅ የኔን ልጅ መትቶት ከሆነ ምች ይምታው፤ የኔ ልጅ ያንቺን ልጅ መትቶት ከሆነ ግን መቼምአለች አሉ አንዷ ፍርደ ገምድል፡፡ ማሰብ ያለብንእኔስ ብሆን? ይሄ ነገር ለኔስ ቢመጣ?...” ብለን ነው፡፡ የኅሊና ፍርድና እውነት ደግሞ ጉልበት ሲሰማን የሚጨቆኑ፣ ገንዘብ ስናገኝ የሚታፈኑ፣ ሥልጣን ሲኖር የሚደፈጠጡ፣ የሰው ምልዓት ሲታይ የሚረሱ ሊሆኑ አይገባም፤ የእውነት አምላክ ስላለ ሁሉን ያያልና፡፡

በግልጽ እንነጋገር፡፡ መሸፋፈን ይቅር፡፡ ሁሉም በጊዜው ይገለጣልና ሃቅን ተመርኩዘን ከአንጀት መነጋገሩ ቅሬታን ለማስወገድ የመጀመሪያ እርምጃ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያን በአንደኛው አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አንድ ሙስሊም ወይም አንድ የፕሮቴስታንት የክርስትና እምነት ተከታይ ገብቶ ካህናትና ምዕመናን በሚመስጥ የስብከት አገልግሎት ላይ እያሉ ይህ ሰውማርያም እንትን ነበረች! እንኳን ልታማልድ ለራሷም አልዳነችም! ከአላህ በቀር እግዚሃር የሚባል የለም! ሁላችሁም …› ቢሉ - በርግጠኝነት ነው የምነግራችሁ - ይህን መሰሉ ሰው እንዳበደ ተቆጥሮ ይታዘንለታል ይጸለይለታልም እንጂ ማንም ዝንቡን እሽ አይለውም፡፡ ምዕመናን በከዘራ ቀሳውስት በመቋሚያ ጨፍጭፈው ይገድሉታል የምትሉ ካላችሁ ተሳስታችኋል፤ ቢያንስ በዚህ ዘመን እንዲህ ያለ ሞኝነት የለም፡፡ የዚህ ዓይነት አጋጣሚዎችን እኔ ራሴ በተገኘሁባቸው የአምልኮት ጊዜዎች ስለታዘብኩ ሰው ከንፈሩን እየመጠጠ ሲያዝን እንጂምናባቱንና ይሄን እንትን ደብድበህ አባርልኝ፤ ወደዚያ አንገቱን ቀንጥስና ገላግልልኝ!› የሚል አንድም ሰው አላየሁም፡፡ ባይሆን ድምጹ የሚረብሽና ፕሮግራምን የሚያሰናክል ከሆነ ዘበኞች ተጠርተው ገፋፍተው እንዲያስወጡት ይደረጋል፡፡

ይህ ለምን ሆነ ስንል አንደኛ ምዕመናን በፈጣሪ ፍርድ መግባት እንደሌለባቸውና መቅጣትም መግደልም ማዳንም መኮነንም የእግዚአብሄር ተግባራት እንደሆኑ ይረዳሉ፤ ሁለተኛ የመጻሕፍት አስተምህሮ ሼህ ኤሊያስ ያላገጡበት ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚያስተምረን ጠላትህን ውደድ፣ ክፉን በክፉ አትቃወም፣ አትግደል፣መጎናጸፊያህን ቢጠይቅ እጀ ጠባብህን ጨምርለትስለሚሉ በነዚህ ተገቢ ሕግጋት አማካይነት ሕዝቡ በፈጣሪ ሥራ እንዳይገባ የለዘበ ስብዕናን ተላብሶኣል፤ ሦስተኛ የመንግሥትን ሕግ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ያም ሕግ ተጠርጣሪ ወንጀለኛንና ጥፋተኛን ይዞ ወደ ሕግ ማቅረብ እንጅ በኦሪታዊ የሀሙራቢዐይንን ለዐይንጥርስን ለጥርስወይም እንደዘመነ ጻፎችና ፈሪሣውያን ስቅሎ፣ ስቅሎየወል ሥርዓተ አልበኝነት አንድ ሰው እንደዐይጥ አይጨፈጭፍም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ኋላ ቀር ፍርድ እጅግ አደገኛና ኃላፊነት የሚወስድን ሰው ደብዛ የሚያጠፋ ከትክክለኛ ስብዕናም የማይመነጭ ደመ ቁጡነት ነው፡፡
እዚህ ላይ አንድ የቆዬ ታሪክ እንይ፡፡ በጥንት ዘመን በግሪክ ሀገር ሁለት ሴና የሚባሉ ታዋቂ ሰዎች ነበሩ፡፡ አንዱ ፈላስፋና ባለቅኔ ነው፡፡ ሌላው የፖለቲካ አማካሪ ነው፡፡

የፖለቲካ አማካሪው ጥፋት አጠፋ ይባልና ሕዝቡ ሊገድለው በስሙ አማካይነት ሲያፈላልግ ያኛውን ሲና ይይዙታል፡፡እንዴ! እኔ እኮ ባለቅኔው ሴና ነኝ!› ቢላቸውግዴለም፣ ሴና በመሆንህ ብቻ እንገድልሃለን!› ብለው ያለጥፋቱ በስሙ ብቻ ገደሉት ይባላል፡፡ ይህ እንግዲህ ማኅበረሰብኣዊ ዕብደት ካልሆነ ሌላ ስም ሊሰጠው አይችልም፡፡ ሞብአደገኛነት እዚህ ላይ ነው፡፡ሞብደግሞ ያውሞብነው - ከሳሽ ተከሳሽ - ዳኛ ጠበቃ ሕግ ፍርድ ቤትየሌለው እጅግ አደገኛ የሀገርና የኅብረተሰብ ጠንቅ ነው፡፡ ይህን መሰሉን ነቀርሣ የሚጠቀሙበት ተንኮለኞችና ሥውር የጥፋት ተልዕኮ የሚያራምዱ ወገኖች ናቸው፡፡ በዚህ ረገድ የሚታየውን አደጋ ለመቀነስና በሂደትም ለማጥፋት ታዲያ ከየሃይማኖት ተቋማቱና ከምሁራን አካባቢ ራሳቸው ቀድመው የነቁ አብቂዎች ያስፈልጉናል - ዐይንን ገላጭ አንቂዎች፡፡ በሀገራችንም ሆነ በመላው ዓለም ይህን መሰሎች የዕብደት ምልክቶች ሞልተዋል፡፡ በጅምላ መፍረድ፣ በጅምላ እያሉ ንጹሓንን መፍጀት፣ በቅድመ አእምሮ ፍርድ በጥላቻ በመሞላት በአንዱ ወገን ላይ መዝመት፣በሃይማኖትና በዘር በቋንቋ ሰበብ ወገንን ማግለል፣እነዚህ ሁሉ ከእውነተኛው የፈጣሪ መንገድ የወጡ ናቸው፡፡  

ከፍ ሲል በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢገኙ ብዬ እንደጠቆምኩት ዓይነት ከጤናማ አካሄድ የወጣ አሠራር በመስጊድ ውስጥ ቢገኝስ ብለን እንጠይቅ፡፡ የምናገኘው ምስል አያስደስተንም፡፡ መናገሩም ይቅርብኝ፡፡ ይሁንና በሀገራችን ይህን መሰሉ አዝማሚያ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ አይስተዋልም ነበር፡፡መቻቻልና በኔ ይቅር ባንተ ይቅር ነግሦ ይታይ ነበር፤ አንዱ የአምልኮ ቤት ሲሠራ ሌላኛው ይረዳው ነበር፡፡ በሩቅ የምንሰማውና የምንታዘበው ክስተት ወደ ሀገራችን እንዳይገባና ሥር እንዳይሰድ ተባብረን ከአሁኑ እናጨንግፈው፡፡ ነገሩ ያደረች ባቄላ ከመሆኑ በፊት ወደቀድሞው ለዘብተኛ አቋማችን እንመለስና ቆም ብለን እንተያይ፡፡ ሌላው ሁሉ ቀርቶ በየትም የሌለ የምግብ ልዩነት ያለው እንኳን እኛ ሀገር ውስጥ ነው፡፡ ይህም ልዩነት የተተከለው ባለማወቅ እንጂ በማወቅ አይመስለኝም - ለነገሩ ብዙም አልለያየንም፡፡

በእምነት ብቻ ሳይሆን በአኗኗርም ብዙ የባህልና የትውፊት መስተጋብሮች ያሉን ሕዝብ ስለሆንን ከፍ ሲል በድርበቡ የገለጥኩትን የመሰለ ከውጪ የመጣ ተፅዕኖ አያዋጣንም ብዬ በሙሉ ልብ ልናገር እወዳለሁ፡፡ የሚያዋጣን እንደስከዛሬው አንዱ ሲያጠፋ ሌላው እየገሰጸና እየመከረ ተግባብቶና ተነፋፍቆ መኖሩ ብቻ ነው፡፡ ይህን የምለው ብዙ ነገር በአእምሮዬ እየተመላለሰ ስለሚያስጨንቀኝ ነው፡፤ የአንዳንድ መጤ አክራሪዎች አካሄድ አላማረኝም፡፡ እነዚህ አክራሪዎች ደግሞ ሳይናገሩ ያስታውቃሉ፡፡ ኢትዮጵያዊውን እስላምና አክራሪውን እስላም በዐይነ ውኃቸው መለየት እንችላለን፡፡ አክራሪው ከፈሱ ጋር የተጣላ ነው፡፡ ከርሱ ጋር ለአንድ ደቂቃ እንኳን መነጋገር አይቻልም፤ የሚቀናው በኪሱ የወተፋትን ጩቤ አውጥቶአላሁዋክበር!› ማለትና ሬሣን አጋድሞ መፎከር ነው፡፡ ይህን መሰሉን አውሬነት በአልቃኢዳ የዩቲዩብ ዘግናኝ ምስል ስለተመለከትኩ ከዚህ ዓይነቱ ዐረመኔ ተግባር ሀገራችንን እንዲጠብቅ በበኩሌ በገራገሮቹ የእስላምና የክርስቲያን የጥንቶቹ አባቶችና እናቶች ስም አምላክን እለምነዋለሁ፤ እናንተም የበኩላችሁን ጸልዩ፡፡

ብዙዎቻችን ወያኔ የሚለውን ሁሉ ላለማመን ቃል አለብን፡፡ የእረኛው ቢጤ እንዳይሆን ግን እሰጋለሁ፡፡ ለዚያ ደግሞ ማስተማመኛ በተለይ ከልሂቃን ሙስሊሞች ብዙ እንጠብቃለን፡፡ እረኛው በጎቹን ቀበሮ እንደበላበት እያስመሰለ ሲጮህና ሰዎቹ እንዲደርሱለት በውሸት ሲያታልል ቆይቶ በመጨረሻው የምር ቀበሮዎች መጥተው ዘነጣጥለውለት ሲሄዱ ቢጮህ አንድም የሚመጣለት ሰው አጣ፡፡ እኛም እንደዚያ እንዳንሆን እፈራለሁ፡፡ ለዚህ መድሓኒቱ ርስ በርስ እንድንፈራራ ያደረገንን ብልሹ የወያኔ ሥርዓት በጋራ አስወግደን የጋራ መተማመን የሚፈጠርበትና አንዱ በሌላው ላይ ሸክም የማይጭንበትን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመሠረትን እንደሆነ ነው፡፡

ኤሎሄ እንበል፡፡የኢትዮጵያ አምላክ ሆይ ጸሎታችንን ስማ፣ በመከራችን ቀን ፊትህን ከኛ አትመልስ፡፡ይህን ደግሞ ልብ እንበል! ሳዑዲ ኢትዮጵያ ውስጥ ከገባች ወዮ ለኛ! ኢራን ኢትዮጵያ ውስጥ ከገባች ወዮ ለኛ! ሦርያ ኢትዮጵያ ውስጥ ከገባች ወዮ ለኛ! አፍጋኒስታን ኢትዮጵያ ውስጥ ከገባች ወዮ ለኛ! ፓኪስታን ኢትዮጵያ ውስጥ ከገባች ወዮ ለኛ! አልሻባብና አልቃኢዳ አል ምናምን ሁላ ተጠራርታ ኢትዮጵያ ውስጥ ከገባች ወዮ ለኛ! “ስለዚህእንበልና ጸሎታችንን እንቋጭ - “ስለዚህ፣ አምላክ ሆይ ለጥፋት ያቆበቆቡ ፀረ - ኢትዮጵያ ኃይሎችን አስታግስልን፤ እስካሁን በደርግና በወያኔ ያየነው አበሳ ከበቂ በላይ ነውና ከአሁን በኋላ ምሕረትህን ላክልን፤ አሜን፡፡

እስላምም ክርስቲያንም ሰላማዊ ሕይወትን ይፈልጋሉ፤ አፈንጋጮችና በአክራሪነት የተሠለፉ ጥቂቶች ብቻ ናቸው በዕልቂትና በመሠያየፍ የሚያምኑ - ደግሞም እነሱ አይደሉም እየሞቱ ያሉት፤ ለዕኩይ ዓላማቸው የሚሞቱላቸውን ንጹሓን ዜጎች ከየሀገሩ እየለቀሙ ያዘጋጃሉ እንጂ እነሱ በምቹ ሥፍራ ተቀምጠው ነው በገንዘባቸው የሚፈልጉትን ሁከት የሚፈጥሩት፡፡ እነሱን የማያውቅ ማን አለ?  አንዷ ሀበሻ ከአንገቷ በስህተት የወጣን የወርቅ መስቀል በጣጥሶ መሬት ላይ በመጣል የሚረጋግጥ መንግሥታዊና ሕገ መንግሥታዊ ድጋፍ ያለው ፖሊስና ወታደር ነው የሚኖርባት - ሳዑዲ! ሌላ ቃል ብትተነፍስማ የሐሙሱ ጎራዴ ነው ተስሎ የሚጠብቃት፡፡ በውኃ ቀጠነ ሰዎች በሚታረዱባት ሀገር አራጆች ከሕግ በላይ እንደሆኑም ይነገራል፤ በዊስኪ መጠጥ ፍጆታ ሳዑዲ ከዓለም ስንተኛ ትሆን? አላውቅም ግን ከደረጃ ሰንጠረዥ እንደማትወጣ እገምታለሁ - ዋናው ነገር ቀን አይጉደልብህ - ድሃ አትሁን፤ ወፍራም ሥልጣንም ይኑርህ፤ ያኔ ዓለም ያንተና የቢጤዎችህ ብቻ ትሆናለች፤ መገደልና መታሠር አንተ በምትጠላቸው ላይ እንጂ ወዳንተ አካባቢ ዝር አይሉም፤ ያሻህን ብትሠራ እንኳን! ብትገድል ሌላ ገዳይ ትሰይማለህ - እንዳስፈላጊነቱ የሚቀጣልህ ወይም የሚወቀስልህ፡፡ ብታጭበረብር ሌላ ምትክ ተጠያቂ ይኖርሃል - ያንተን አበሳ በሙሉም ሆነ በከፊል ወስዶ ዕዳህን የሚከፍልልህ - ሊያውስ ተጠያቂ ስትሆን አይደል? አንተ በቀን 24 ጊዜ የምታደርገው ተራ ነገር ድሃው በአሥር ዓመት አንዴ ቢያደርግ እሱ ወንጀለኛ ነውና ይገደላል ወይ ይታሰራል፤ አንተ ግን ንጹሕ መልአክ ነህ፡፡ አየሃት የዚህችን ዓለም ነገር? ያልተማርክና በጭካኔህ የለየለት ዐውሬ ብትሆንም እንኳን ባለክብር ዶክትሬትና ሩህሩህ ባለራዕይ የሀገር አለኝታ ነህ፡፡ ባጭሩ ካለህ አለህ፤ ከሌለህ የለህም፡፡ ይህች ምድርና ነዋሪዎቿ እጅግ ያሳዝናሉ፡፡ የፊጥኝ ታስረው የተያዙት በማን እንደሆነ ስንገምተውና ስንረዳው ደግሞ ይበልጥ ስፍስፍ ልንልላቸው እንገደዳለን፤ ሁላችን በአንድ ወይ በሌላ አስቀያሚ ሁኔታ የታሠርንባት የመከራና የሥቃይ ዓለም ናት፡፡ ማንኛችንም መረዳት ያለብን ነገር ኢትዮጵያ የሁሉም መሆኗን ነው፡፡ የሁሉ እንዳትሆን የሚሠሩ ካሉ ፈጣሪ ሤራቸውን ያክሽፍባቸው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በደምሳሳው የዋህና እንግዳ ተቀባይ ነው፤ ይህ ባሕርይው ግን ሊያስጠቃው አይገባም፡፡ በደካማ ጎኑ ገብተው ሊጎዱት የሚፈልጉ የውጭ ኃይሎች ይኖራሉና ፈጣሪ የሥራቸውን ይስጣቸው - ከውስጥ ተባባሪዎቻቸው ጭምር፡፡  

ሃይማኖትን ማስፋፋት በራሱ መጥፎ አይደለም፡፡ ነገር ግን የምታስፋፋበት መንገድ ነው ሊፈተሸና የአካሄድ እርምት ሊደረግለት የሚገባ፡፡ በራስ ሀገር ቤተ ክርስቲያን ቀርቶ በቤትህ ውስጥ ማምለክ እንዳትችል እየተከለከልክና በሞት እየተቀጣህ በሰው ሀገር ገብተህ በሠይፍና በጎራዴ ሃይማኖትን ለማስፋፋት መሞከር ሰይጣናዊነት እንጂ የደግ መንፈስ ውጤት ሊሆን አይችልም፡፡ በዓለም ብዙ ፍርደገምድልነት ይታያል፡፡ ብዙ ያናግራል፤ ግን ለአንድዬ እንተወው፡፡ ዛሬ ዛሬን ይመስላል፡፡ ነገ ግን የተለዬ ይሆናል፡፡ ሁሉም እንደሥራው ማግኘቱ ቀድሞ የተነገረ ነውና ክፉም ለራስ ደግም ለራስ የሚለውን አንዘንጋ፡፡ ፈጣሪ ለኢትዮጵያ የሚበጀውን ያምጣልን፤ ሰላም፡፡


ዳግማዊ ጉዱ ካሣ